Monday, January 18, 2021


🗣በብርሃኑ(ምሕረት የበዛለት)
👉በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሁለት ዓይነት አስተምህሮ እንዳለ ባለፈው ፅሁፌ ገልጨላችሁ ነበር።እነዚህም፦ አንፅሓ እና ዐቀባ የሚባሉ ናቸው።አንፅሓ የሚባሉት ነበረባት በመልአኩ ብሥራት ጊዜ ነፃች ሲሉ ዐቀባዎች ግን ከእናቷ ማኅፀን ጀምሮ ከጥንተ አብሶ ተጠብቃለች የሚሉ ናቸው።
👉አልነበረባትም ለሚሉ ሰዎች የተወሰኑ ጥያቄዎችን ልጠይቅና ነበረባት ግን ነፅታለች የሚሉ አባቶችን ሀሳብ አቀርባለሁ።
1- ድንግል ማርያም የአዳም ልጅ አይደለችምን? ከሆነችስ ያለ ልዩነት "በአንዱ አለመታዘዝ ብዙዎች ኃጢአተኞች ሆኑ" የሚለው ቃል እንዴት አይመለከታትም?
2- የጌታ መሞትና ማዳን እርስዋን የማይመለከት ነውን? ጌታ ለእርስዋም ካልሞተ "መድኃኒቴ" ለምን አለችው?
3- እርስዋን ጥንተ አብሶ ካለባት እናቷ ያለ ጥንተ አብሶ እንድትወለድ ካደረገ ክርስቶስስ ጥንተ አብሶ ካለባት እናቱ ንፁህ ሆኖ መወለድ አይችልምን?
1- ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ በመመረቂያ ፅሁፋቸው እንዲህ አሉ፦ "እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ድንግል ማርያም ለእግዚአብሔር የመታዘዝና የእምነት አርኣያና ምሳሌ ናት።በሁለት ወገን ድንግል ናት።በሥጋም በነፍስም።#የተፀነሰችው_ያለ_ጥንተ_አብሶ ወይም #ከጥንተ_አብሶ_ነፃ_ናት" #ባንልም ቅሉ ቅድስተ ቅዱሳን ንፅህት በእግዚአብሔር የማዳን ሥራና በሥጋዌው ሱታፌ ያላት ናት።" ወልታ ፅድቅ.ገፅ.192-193
2- መጋቤ ብሉይ ሰይፈ ሥላሴ ዮሐንስ የተባሉ ሊቅ በ "መሰረተ ሃይማኖትና የካህናት ተልእኮ" በሚለው መፅሐፋቸው ገፅ.29 ላይ፦ "አንዳንዶች እመቤታችን አድፎ የነበረው የአዳም ጠባይ ወይም #ጥንተ_አብሶ_እንደሌለባት_ያስተምራሉ፤ነገር ግን ይሄ ትምህርት በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያናችን #ተቀባይነት_የለውም።ምክንያቱም እመቤታችን ከኢያቄም ከሐና በሕጋዊ ሩካቤ የተገኘች ናት። #ካሣ_የማያሳስፈልጋትም_ሳትሆን_ክርስቶስ_በደሙ_ከዋጃቸው_ካሣም_ከተከፈለላቸው_ወገን_ናት፤ሆኖም እንደ አዳምና ሔዋን የምኞት የመናገርና የገቢር ኃጢአት ፈፅሞ የለባትም።" ብለዋል።
3- አሥራት ገብረማርያም በትምህርተ መለኮት መፅሐፋቸው #1983ቱ እትም ገፅ.96 ላይ ፦ "በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እምነት መሰረት በሉቃ.1:38 ላይ የመልአኩን ብሥራት ተቀብላ "እነሆኝ የጌታ ባሪያ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ" ብላ እምነቷን በእግዚአብሔር ላይ ባሳረፈች ጊዜ ጌታን ከመውለዷ በፊት መንፈስ ቅዱስ እመቤታችንን ቀድሶና #አንፅቶ_የጥንቱን_የአዳምን_ኃጢአት አስወግዶላታል።……በሌላ በኩል ደግሞ የቀድሞው የአዳም ኃጢአት የሚወረሰው በወንድ ዘር አማካኝነት ልጅ በሚወለድበት ጊዜ ከአባት ወደ ልጅ በመሆኑና ጌታ ግን የተወለደው መንፈስ ቅዱስ #የጥንቱን_ኃጢአት_ካስወገደላት ከእናት ብቻ ስለሆነ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣውን የጥንቱን የአዳም ኃጢአት አልወረሰም።"
የአቡነ ሺኖዳንና የምሥራቃውያንን እንዲሁም የኢትዮጵያን ጥቂት ሀሳብ በክፍል ሁለት እጨምርበታለሁ።
ሻሎም!!
Zerubbabel To Belong Jesus, ዮኒ ጌጡ and 5 others
1 Comment

No comments:

Post a Comment