1
1


ጳጳሳት ያግቡ!
በቤተ ክርስቲያን ያለው ሥርዓት ጳጳስ ለመሆን የሚገባው ሰው በትዳር ያልተጠላለፈ መሆን አለበት የሚል ነው፡፡ በዚህም የተነሣ በምንኩስና ሕይወት ጸንቶ የኖረና ትዳርም ሆነ ልጅ የሌለው ሰው ነው የጵጵስናዋን ክብር የሚያገኘው፡፡ ይህ ሥርዓት ግን ‹‹ ‹ጵጵስናን ሊሾም የሚወድ መልካም ሥራን ወደደ› የሚለው ቃል የታመነ ነው፡፡ ነገር ግን ጵጵስናን የሚሾም እንዲህ ሊሆን ይገባዋል፡- የማይነቀፍ÷ አንዲት ሴት ያገባ÷ ትጉህ ሰው÷ ብልህ÷ እንደሚገባው የሚሠራ÷ እንግዳ ተቀባይ÷ ራሱን የጠበቀ÷ የሚያስተምርና የሚገስጽ÷ የማይሰክር÷ ለመማታት እጁን የማያፈጥን÷ ነገር ግን ትዕግሥተኛ÷ የማይጣላና ገንዘብን የማይወድ÷ የቤቱን አስተዳደር በመልካም የሚያስተዳድር÷ በፍጹም ንጽሕና የሚታዘዙ ልጆች ያሉት፡፡ ቤቱን ማስተዳደር የማይችል ሰው የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን እንዴት ያስተዳድራል?›› ከሚለው ጋር የማይስማማ ነው (1ኛ ጢሞቴዎስ 3÷1-5 - የ2000 ዕትም)፡፡ ከዚህም ጋር ብቻ ሳይሆን ከዲድስቅልያም ጋር አይስማማም፡፡ ዲድስቅልያ፤ ‹‹እንደዚህ ያለ ኤጲስ ቆጶስ አንዲት ሴት ያግባ ቤተ ሰቦቹን በመልካም ማስተዳደር የሚችል፣ የሚያስተምር የሚመክርና ልጆቹን በንጽሕና ያሳደገ ይሾም›› ይላልና (መጽሐፈ ዲድስቅልያ አንቀጽ 4 ቊጥር 12)፡፡ በሐዋርያው ጳውሎስም ሆነ በዲድስቅልያ ትእዛዝ መሠረት አሁን ቤተ ክርስቲያንን በማስተዳደር ላይ ያሉት ሰዎች ቤተ ክርስቲያንን ለማስተዳደር ብቁ አይደሉም ማለት ነው፡፡ ጳጳሳት ማግባታቸው ለእነርሱም ሆነ ለቤተ ክርስቲያን መልካም ነው፡፡ ሰይጣን አገልጋዮችን ከሚፈትንበትና ብዙዎችም ከወደቁበት ወጥመድ ውስጥ አንዱ የዝሙት ፈተና ነው፡፡ ..ለዚህ ደግሞ ሁነኛው መፍትሔ ባለ ትዳር መሆንና ለአገልግሎት በሚንቀሳቀሱበት ስፍራ ሁሉ የትዳር አጋራቸውን ይዘው መንቀሳቀስ መቻል ነው፡፡ ይህም ደግሞ ሰዎች በእነርሱ እንዳይፈተኑ እና እነርሱ ራሳቸውም በወሲባዊ ፍላጎት እንዳይፈተኑ ይረዳል፡፡ ‹‹ስለ ዝሙት ጠንቅ ለእያንዳንዱ ለራሱ ሚስት ትኑረው ለእያንዳንዲቱ ደግሞ ለራስዋ ባል ይኑራት›› ተብሎ እንደተጻፈው (1ኛ ቆሮንቶስ 7÷2)፡፡
በቤተ ክርስቲያን ያለው ሥርዓት ጳጳስ ለመሆን የሚገባው ሰው በትዳር ያልተጠላለፈ መሆን አለበት የሚል ነው፡፡ በዚህም የተነሣ በምንኩስና ሕይወት ጸንቶ የኖረና ትዳርም ሆነ ልጅ የሌለው ሰው ነው የጵጵስናዋን ክብር የሚያገኘው፡፡ ይህ ሥርዓት ግን ‹‹ ‹ጵጵስናን ሊሾም የሚወድ መልካም ሥራን ወደደ› የሚለው ቃል የታመነ ነው፡፡ ነገር ግን ጵጵስናን የሚሾም እንዲህ ሊሆን ይገባዋል፡- የማይነቀፍ÷ አንዲት ሴት ያገባ÷ ትጉህ ሰው÷ ብልህ÷ እንደሚገባው የሚሠራ÷ እንግዳ ተቀባይ÷ ራሱን የጠበቀ÷ የሚያስተምርና የሚገስጽ÷ የማይሰክር÷ ለመማታት እጁን የማያፈጥን÷ ነገር ግን ትዕግሥተኛ÷ የማይጣላና ገንዘብን የማይወድ÷ የቤቱን አስተዳደር በመልካም የሚያስተዳድር÷ በፍጹም ንጽሕና የሚታዘዙ ልጆች ያሉት፡፡ ቤቱን ማስተዳደር የማይችል ሰው የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን እንዴት ያስተዳድራል?›› ከሚለው ጋር የማይስማማ ነው (1ኛ ጢሞቴዎስ 3÷1-5 - የ2000 ዕትም)፡፡ ከዚህም ጋር ብቻ ሳይሆን ከዲድስቅልያም ጋር አይስማማም፡፡ ዲድስቅልያ፤ ‹‹እንደዚህ ያለ ኤጲስ ቆጶስ አንዲት ሴት ያግባ ቤተ ሰቦቹን በመልካም ማስተዳደር የሚችል፣ የሚያስተምር የሚመክርና ልጆቹን በንጽሕና ያሳደገ ይሾም›› ይላልና (መጽሐፈ ዲድስቅልያ አንቀጽ 4 ቊጥር 12)፡፡ በሐዋርያው ጳውሎስም ሆነ በዲድስቅልያ ትእዛዝ መሠረት አሁን ቤተ ክርስቲያንን በማስተዳደር ላይ ያሉት ሰዎች ቤተ ክርስቲያንን ለማስተዳደር ብቁ አይደሉም ማለት ነው፡፡ ጳጳሳት ማግባታቸው ለእነርሱም ሆነ ለቤተ ክርስቲያን መልካም ነው፡፡ ሰይጣን አገልጋዮችን ከሚፈትንበትና ብዙዎችም ከወደቁበት ወጥመድ ውስጥ አንዱ የዝሙት ፈተና ነው፡፡ ..ለዚህ ደግሞ ሁነኛው መፍትሔ ባለ ትዳር መሆንና ለአገልግሎት በሚንቀሳቀሱበት ስፍራ ሁሉ የትዳር አጋራቸውን ይዘው መንቀሳቀስ መቻል ነው፡፡ ይህም ደግሞ ሰዎች በእነርሱ እንዳይፈተኑ እና እነርሱ ራሳቸውም በወሲባዊ ፍላጎት እንዳይፈተኑ ይረዳል፡፡ ‹‹ስለ ዝሙት ጠንቅ ለእያንዳንዱ ለራሱ ሚስት ትኑረው ለእያንዳንዲቱ ደግሞ ለራስዋ ባል ይኑራት›› ተብሎ እንደተጻፈው (1ኛ ቆሮንቶስ 7÷2)፡፡
See Less
99
24 Comments
28 Shares
Like
Comment
Share
Comments
View 14 more comments
- ወዳጄ እኔ ክርስቶስን እንደመሰልኩ እናንተ እኔን ምሰሉ ያለው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ሚስት አግብቶ ነው??? ከጽሑፍህ ምን እንደተረዳው ታውቃለህ ባለህበት ሃይማኖት ጳጳስ ለመሆን አስበሃል የፍትወቱ ነገርም አላስችል ብሎሃል መቼም በተዋህዶ ቤት ሁለት ሆኖ መኖር አይቻልም ጵጵስና የፈለገ እራሱን ለክርስቶስ ጃንደረባ ያድርግ ማግባት ከፈለገ ምዕመን ከተማረ ደግሞ ካህን ይሆናል ይህ ግን ላንተ አለተፈቀ…See More
- Like
- · Reply
- · 2y
- Eni milik hawariyat kerstosn kagnut bewala mist agbtwal endi? Rasachewn janderba nw yadergut enji keza bealm zuriya astmaru bastmarubtm bota menberu bensu tesym washew endi? Epis kopos lemhon be nhitna yenor nekfita yelilbet senay megbar yalw mehon al…See More
- Like
- · Reply
- · 2y
- ኣረ እባካችሁ ማሠብ መሥተዋል ከተውነ ቆየን "ክፋው አውሬ ዲያቢሎስ" ቤቱ አደረገን ማንኛው ፈላስፋ ነህ እባክህ ሠይጣን ለአመሉ መፅሀፍ-ቅዱስ ይጠቅሳል ድብቅ አጀንዳህን እዛው ማመን መታመን እንጅ ፍላጎት አይደለም አራሡን እንዲመቸው አኔ በማለት ነው ሣጥናኤል የወደቀው ያንተን መሥፈርት ተወው
- Like
- · Reply
- · 2y
- ከአባቶች ልትማር ይስፈልግኃል እንጅ የአንቴን የዝሙት ወሬ ቃሉን በማጣመም አትድከም !!
- Like
- · Reply
- · 2y
- Almagbatem eko geta yefqedew new yemilwen alnbebkem zq belo .abo tegermalek .kageba yalgeba mulu tekuretun grtan yasdestal yagrbama ena ena ant enwqwalen bezuriyachen .agebeto pipesna mnm layhon yechelal gn kagebaw yelq yalgebaw legeta giza yestal. Mn …See More
- Like
- · Reply
- · 2y
No comments:
Post a Comment