May 7, 2018
አቡነ ሀብተማርያም
፩ – የትውልድ ታሪካቸው
የቅዱስ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም ትውልድ ሀገር የራውእይ የምትባል ምስራቃዊት ሀገር ውስጥ ሲሆን የኢትዮጵያ ንጉስ እስክንድር በነገሰ በሺ አራት መቶ ሰማንያ ስድስት ዓመተ ምህረት ፍሬ ብሩክ የሚባል አንድ ሰው በዚች ሀገር ውስጥ ነበር፡፡ ይኸውም ከከበሩም ሰዎች ተለይቶ ብዙ ገንዘብ ያለው ባለጸጋ ነበር፡፡ በህጋዊ ጋብቻ ስሟ ዮስቴና የምትባል ሴት አገባ ይህችውም ሴት በደግ ሥራ ሁሉ የተሸለመች ያጌጠች ነበረች፡፡ እነዲህ ባለ ሥራ ሳለች መንፈሳዊ ሀሳብ እንዲህ ሲል ተነሳባት ለአንቺ በዚህ ዓለም መኖር ምን ይረባሻል ዛሬ የሚያልፍ የሚጠፋ ነውና የሚመሰገንበት ለዘለዓለም የሚኖር የማያልፍ ሌላ ዓለም ይገለጣልና % ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌል “ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢገዛ ቢነዳ በነፍሱ ከተጎዳ ምን ይጠቅመዋል እንዳለ” ማቴ. 16÷26፣ ማር. 10÷36፡፡ ለአንቺ ግን በሰማይ ፀንቶ መኖርን ሁለተኛዋን ሀገር መያዝ ይሻላል የሚል ሀሳብ መጣባት፡፡ ይህን ካሰበች በኋላ ፈጥና ተነስታ በሌሊት ከቤት በመውጣት በሀገሯ አንፃር ትይዩ ወደ ሆነው ከጅቦች፣ ከነብሮች፣ ከዓሳማዎች፣ ከጦጦችና ከዝንጀሮዎች በስተቀር ምንም ምን ወደ ማይኖርበት በረሀ ደረሰች፡፡ በዚያም ደጃፏ ያልተዘጋ ትንሽ ዋሻ አገኘች፡፡ በዋሻው ውስጥም መዝሙረ ዳዊትን በአንክሮ የሚደግም ክቡር ባህታዊ አየች ባየችውም ጊዜ ደነገጠች እርሱም ሴቲቱን ባያት ጊዜ ፍርሀት መንቀጥቀጥ በላዩ ላይ ወረደበት፡፡ መጀመሪያ ስትገባ የጋኔን ምትሀት መስላው ነበርና ሰው መሆኗን ባወቀና በተረዳ ጊዜ ተቆጣት፡፡ እሷም ቤቴን ንብረቴን ያለኝን ሁሉ ትቼ መጥቻለሁ በዓለም ውስጥ ያለውን ሁሉ ንቄ እመንን ዘንድ እወዳለሁና ስለዚህም ወደዚህ ምድረበዳ መጣሁ አለችው፡፡ ይህም ባህታዊ በትህትናና በፈሪሀ እግዚአብሔር ይህን የሚያስደንቅ መልካም መልስ በመለሰችለት ጊዜ አንድ ሰዓት ያህል ካሰበ በኋላ ምንኩስናስ የለሽም ነገር ግን በፍቅር በአንድነት ወደ ቤትሽ ወደ ህጋዊ ባልሽ በሰላም ተመለሽ የተፈቀደልሽን እነግርሻለሁ ከህጋዊ ባለቤትሽ ወንድ ልጅን ትወልጃለሽ እርሱም ለዓለም ሁሉ የሚጠቅም ይሆናል የገድሉና የትሩፋቱ ዜና እስከ ዓለም ዳርቻ ይደርሳል በህይወተ ስጋ ሳለ በፈጣሪው እግዚአብሔር ፍቃድ የብዙዎችን ሰዎች ነፍሳት ከሲኦል ያወጣል እንደ መላእክትም ክንፈ ፀጋ ተሰጥቶታል፤ በሰው አካል ከስጋ ሆኖ ሳለ በተመስጦ ወደ ሰማይ የሥላሴን የአንድነትን የሦስትነትን ምስጢር ያያል አላት፡፡ ቅድስት ዮስቴናም ከአረጋዊ ባህታዊው ይህን ነገር ሰምታ አደነቀች የፈጣሪዬ ፈቃድ ከሆነ ወደ ቤቴ እመለሳለሁ አለች፡፡ ጥቂት ወራት ከቆየችም በኋላ መልኩ እንደ በረዶ ነጭ እንደ ፅጌረዳም ብሩህ ቀይ የሆነ መልከ መልካም ገፁ ብሩህ የሆነ ልጅ ወለደች ይህ ህፃን በግንቦት ወርህ በ26 ቀን በተወለደ ግዜ በአባቱና በእናቱ ቤት ታላቅ ደስታ ሆነ፡፡ ይህ ቅዱስ ህፃንም 40 ቀን በሞላው ጊዜ በኦሪትና በሉቃስ ወንጌል እንደተፃፈ በእግዚአብሔር ፊት ያቆሙት ዘንድ ወደ ካህን አቀረቡት፡፡ ክህኑም ለክርስትና አባቱ አሳልፎ ሰጠው ስሙንም ሀብተማርያም ብሎ ሰየመው ከዚህም በኋላ እናት አባቱም ተመለሱ፡፡ ይህ ቅዱስ ህፃን እግዚአብሔርን በመፍራት አደገ ከዕለታት አንድ ቀን ካህናቱ በቤተክርስቲያን ምህላ ሲያደርሱእግዚኦ መሀረነ ክርስቶስ እያሉ ሲፀልዩ ሰምቶ በልቡ ይህች ፀሎት በጣም ጥሩ መልካም ፀሎት ናት እኔ ይህችን ፀሎት መርጫታለሁ በዚህ ዓለም ከአሳች ህሊና በሚመጣውም ዓለም ከገሀነም እሳት እንድንድንባት አውቃለሁ አለ ስግደትንም እንደፈጣን ፈረስ ሩጫ ብዙ እስኪያልበው ድረስ ይሰግድ ነበር፡፡
፪ – አባታችን አቡነ ሀብተማርያም በሕይወት ሳሉ ካረፉም በኃላ ያደረጉት ተአምራት
አባታችን አቡነ ሀብተማርያም በሕይወት ሳሉም ሆነ ካረፉ በኋላ እጅግ ብዙ የሆኑ ተአምራትን አድርገዋል፡፡ ከነዚህ መካከልም በጥቂቱ እንመልከት፡፡ የአቡነ ሀብተማርም አባት ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያምን ከዕለታት በአንድ ቀን የበግ ጠባቂ አደረጓቸው፡፡ እግዚአብሔር ግን በኋላ ለብዙዎች ቅዱሳንና በዓለም ለሚኖሩ ምዕመናን በጎቹ ጠባቂ ያደርገው ዘንድ ወዶ መርጦታልና ያቀን እስኪደርስ ፈጣሪያችን ሀብትማርያምን ይጠብቀው ነበር በዚህም ዕለት በጎች ሲጠብቅ ብዙ የሚሆኑ የበጎች እረኞች እሸት ተሸክመው መጥተው ና እሸትን እንብላ አሏቸው፡፡ አባታችን አቡነ ሀብተምርያም ግን እኔስ አልበላም አሏቸው፡፡ እነርሱ እኛ ብላ ስንልህ ስለምን አትበላም አሉት አባትችንም ይህንን እሸት ከየት እንዳመጣችሁት ምንም እንደሆነ ስለማላውቅ ነው አላቸው (መጽሐፍ ኅጥእ ሰው እግዚአብሔርን የሚፈራውን ይንቀዋል ያቀልለዋል ብሎ እንደተናገረው) እረኞቹም አባታችንን በቁጣ ዓይን አዩዋቸው ብዙም ተቀጣጡባቸው ከዚህም በኋላ ከፊታቸው ተቀምጠው ያን ሰርቀው ያመጡትን እሸት መብላት ጀመሩ እሸቱንም በልተው ከጨረሱ በኋላ አባታችን ቅዱስ ሀብተማርያም በእነዚያን በግ ጠባቂዎችን የማንችለው ፅኑ ዝናብ መጥቷልና ወደየቤታችን እንግባ ከዚህም የምንጠጋበት ቤት ወይም ዋሻ የለምና አላቸው እረኞቹም ለኛ የማይታይ ለአንተ እንዴት ይታያል ብለው ተሳለቁባቸው፡፡
ቅዱስ ሀብተማርያምም የጥበብ አምላክ ልቡን በፀጋ መንፈስ ቅዱስ አበርትቶታልና እኔ የማውቀውን እናንተ አታውቁም ነገር ግን ወደየቤታችሁ ተመልሳችሁ በጊዜ ግቡ አሏቸው እነርሱም አንተ እራስህ ተመልሰህ ወደ ቤትህ ግባ እኛ ግን ፀሀይ ገና ቀትር እያለ ተመልሰን ወደ ቤታችን አንገባም አሉት፡፡ ይህንንም ባሉት ጊዜ በፍጥነት እየሮጠ በጎቹንም እያስሮጠ ወደ ቤቱ ገባ፡፡ ወደ ቤቱም ከገባ በኋላ ፅኑ ዝናብ መጣ ንፋስም ነፈሰ እነዛም አረኞች ይህ ሁሉ በላያቸው ላይ እየተፈፀመ ሳለም አልሸሹም ነበር፡፡ እግዚአብሄርም ክፋታቸውን አስቦባቸዋልና በላያቸው ላይ የጥፋት ውሀ አወረደባቸው ሁላቸውም ይህንን የጥፋት ውሀ እስኪፈፀምባቸው ድረስ አልተነቃነቁም ነበርና ሁሉም አለቁ፡፡
በዚህም ሌሊት ቃል ከሰማይ ሶስት ጊዜ ሀብተማርያም ሀብተማርያም ሲል ጠራው ይህም ህፃን አባቱ በአጠገቡ ተኝቶ ነበርና አባቱ የጠራው መስሎት አባቴ ሆይ አለሁ ሲል መለሰ፡፡ ይህንንም ማለቱ ቀድሞ በኤሊ ሊቀ ካህናት ጊዜ እንደተፈፀመ ሆኖበት ነው ሳሙ. 3÷3፡፡ እንደዚህም ሁሉ እግዚአብሔር ይህንን ህፃን ሀብተማርያም እያለ ሶስት ጊዜ ጠራው፡፡ ህፃኑም ሀብተማርያም ተነስቶ ታጥቆ እጅ ነስቶ እንደ ሳሙኤል ጌታዬ ባርያህ ይሰማል በል ተናገር አለው፡፡
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ከአሁን ጀምሮ ግን በግ ጠባቂዎች ከእርሻቸው ያልሆነውን ከሌላ እርሻ የሆነውን እሸት አምጥተው ብላ ቢሉህ አልበላም በላቸው፡፡ እናንተ ግን ብትወዱ ሄዳችሁ ብሉ በኋላ ግን ገሀነም ትገባላችሁ በእሳት ትቃጠላላችሁ በላቸው እንተን ግን ለሚሰሙ ለመረጥካቸው ቃሉን ትነግራቸው ዘንድ ከእኔ ጋር በሚስጢር ትነጋገር ዘንድ መርጬሃለሁ አለ፡፡ አቡነ ሀብተማርያምም ለቃልህ እታዘዝ ዘንድ እሺ ብያለሁ አለው የጠራውም ቃል ስሜንም በኋላ እነግርሃለሁ ነገር ግን የምልህን ቃልና ትዕዛዝ ጠብቅ አለው ዮሐ.
፩ – የትውልድ ታሪካቸው
የቅዱስ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም ትውልድ ሀገር የራውእይ የምትባል ምስራቃዊት ሀገር ውስጥ ሲሆን የኢትዮጵያ ንጉስ እስክንድር በነገሰ በሺ አራት መቶ ሰማንያ ስድስት ዓመተ ምህረት ፍሬ ብሩክ የሚባል አንድ ሰው በዚች ሀገር ውስጥ ነበር፡፡ ይኸውም ከከበሩም ሰዎች ተለይቶ ብዙ ገንዘብ ያለው ባለጸጋ ነበር፡፡ በህጋዊ ጋብቻ ስሟ ዮስቴና የምትባል ሴት አገባ ይህችውም ሴት በደግ ሥራ ሁሉ የተሸለመች ያጌጠች ነበረች፡፡ እነዲህ ባለ ሥራ ሳለች መንፈሳዊ ሀሳብ እንዲህ ሲል ተነሳባት ለአንቺ በዚህ ዓለም መኖር ምን ይረባሻል ዛሬ የሚያልፍ የሚጠፋ ነውና የሚመሰገንበት ለዘለዓለም የሚኖር የማያልፍ ሌላ ዓለም ይገለጣልና % ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌል “ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢገዛ ቢነዳ በነፍሱ ከተጎዳ ምን ይጠቅመዋል እንዳለ” ማቴ. 16÷26፣ ማር. 10÷36፡፡ ለአንቺ ግን በሰማይ ፀንቶ መኖርን ሁለተኛዋን ሀገር መያዝ ይሻላል የሚል ሀሳብ መጣባት፡፡ ይህን ካሰበች በኋላ ፈጥና ተነስታ በሌሊት ከቤት በመውጣት በሀገሯ አንፃር ትይዩ ወደ ሆነው ከጅቦች፣ ከነብሮች፣ ከዓሳማዎች፣ ከጦጦችና ከዝንጀሮዎች በስተቀር ምንም ምን ወደ ማይኖርበት በረሀ ደረሰች፡፡ በዚያም ደጃፏ ያልተዘጋ ትንሽ ዋሻ አገኘች፡፡ በዋሻው ውስጥም መዝሙረ ዳዊትን በአንክሮ የሚደግም ክቡር ባህታዊ አየች ባየችውም ጊዜ ደነገጠች እርሱም ሴቲቱን ባያት ጊዜ ፍርሀት መንቀጥቀጥ በላዩ ላይ ወረደበት፡፡ መጀመሪያ ስትገባ የጋኔን ምትሀት መስላው ነበርና ሰው መሆኗን ባወቀና በተረዳ ጊዜ ተቆጣት፡፡ እሷም ቤቴን ንብረቴን ያለኝን ሁሉ ትቼ መጥቻለሁ በዓለም ውስጥ ያለውን ሁሉ ንቄ እመንን ዘንድ እወዳለሁና ስለዚህም ወደዚህ ምድረበዳ መጣሁ አለችው፡፡ ይህም ባህታዊ በትህትናና በፈሪሀ እግዚአብሔር ይህን የሚያስደንቅ መልካም መልስ በመለሰችለት ጊዜ አንድ ሰዓት ያህል ካሰበ በኋላ ምንኩስናስ የለሽም ነገር ግን በፍቅር በአንድነት ወደ ቤትሽ ወደ ህጋዊ ባልሽ በሰላም ተመለሽ የተፈቀደልሽን እነግርሻለሁ ከህጋዊ ባለቤትሽ ወንድ ልጅን ትወልጃለሽ እርሱም ለዓለም ሁሉ የሚጠቅም ይሆናል የገድሉና የትሩፋቱ ዜና እስከ ዓለም ዳርቻ ይደርሳል በህይወተ ስጋ ሳለ በፈጣሪው እግዚአብሔር ፍቃድ የብዙዎችን ሰዎች ነፍሳት ከሲኦል ያወጣል እንደ መላእክትም ክንፈ ፀጋ ተሰጥቶታል፤ በሰው አካል ከስጋ ሆኖ ሳለ በተመስጦ ወደ ሰማይ የሥላሴን የአንድነትን የሦስትነትን ምስጢር ያያል አላት፡፡ ቅድስት ዮስቴናም ከአረጋዊ ባህታዊው ይህን ነገር ሰምታ አደነቀች የፈጣሪዬ ፈቃድ ከሆነ ወደ ቤቴ እመለሳለሁ አለች፡፡ ጥቂት ወራት ከቆየችም በኋላ መልኩ እንደ በረዶ ነጭ እንደ ፅጌረዳም ብሩህ ቀይ የሆነ መልከ መልካም ገፁ ብሩህ የሆነ ልጅ ወለደች ይህ ህፃን በግንቦት ወርህ በ26 ቀን በተወለደ ግዜ በአባቱና በእናቱ ቤት ታላቅ ደስታ ሆነ፡፡ ይህ ቅዱስ ህፃንም 40 ቀን በሞላው ጊዜ በኦሪትና በሉቃስ ወንጌል እንደተፃፈ በእግዚአብሔር ፊት ያቆሙት ዘንድ ወደ ካህን አቀረቡት፡፡ ክህኑም ለክርስትና አባቱ አሳልፎ ሰጠው ስሙንም ሀብተማርያም ብሎ ሰየመው ከዚህም በኋላ እናት አባቱም ተመለሱ፡፡ ይህ ቅዱስ ህፃን እግዚአብሔርን በመፍራት አደገ ከዕለታት አንድ ቀን ካህናቱ በቤተክርስቲያን ምህላ ሲያደርሱእግዚኦ መሀረነ ክርስቶስ እያሉ ሲፀልዩ ሰምቶ በልቡ ይህች ፀሎት በጣም ጥሩ መልካም ፀሎት ናት እኔ ይህችን ፀሎት መርጫታለሁ በዚህ ዓለም ከአሳች ህሊና በሚመጣውም ዓለም ከገሀነም እሳት እንድንድንባት አውቃለሁ አለ ስግደትንም እንደፈጣን ፈረስ ሩጫ ብዙ እስኪያልበው ድረስ ይሰግድ ነበር፡፡
፪ – አባታችን አቡነ ሀብተማርያም በሕይወት ሳሉ ካረፉም በኃላ ያደረጉት ተአምራት
አባታችን አቡነ ሀብተማርያም በሕይወት ሳሉም ሆነ ካረፉ በኋላ እጅግ ብዙ የሆኑ ተአምራትን አድርገዋል፡፡ ከነዚህ መካከልም በጥቂቱ እንመልከት፡፡ የአቡነ ሀብተማርም አባት ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያምን ከዕለታት በአንድ ቀን የበግ ጠባቂ አደረጓቸው፡፡ እግዚአብሔር ግን በኋላ ለብዙዎች ቅዱሳንና በዓለም ለሚኖሩ ምዕመናን በጎቹ ጠባቂ ያደርገው ዘንድ ወዶ መርጦታልና ያቀን እስኪደርስ ፈጣሪያችን ሀብትማርያምን ይጠብቀው ነበር በዚህም ዕለት በጎች ሲጠብቅ ብዙ የሚሆኑ የበጎች እረኞች እሸት ተሸክመው መጥተው ና እሸትን እንብላ አሏቸው፡፡ አባታችን አቡነ ሀብተምርያም ግን እኔስ አልበላም አሏቸው፡፡ እነርሱ እኛ ብላ ስንልህ ስለምን አትበላም አሉት አባትችንም ይህንን እሸት ከየት እንዳመጣችሁት ምንም እንደሆነ ስለማላውቅ ነው አላቸው (መጽሐፍ ኅጥእ ሰው እግዚአብሔርን የሚፈራውን ይንቀዋል ያቀልለዋል ብሎ እንደተናገረው) እረኞቹም አባታችንን በቁጣ ዓይን አዩዋቸው ብዙም ተቀጣጡባቸው ከዚህም በኋላ ከፊታቸው ተቀምጠው ያን ሰርቀው ያመጡትን እሸት መብላት ጀመሩ እሸቱንም በልተው ከጨረሱ በኋላ አባታችን ቅዱስ ሀብተማርያም በእነዚያን በግ ጠባቂዎችን የማንችለው ፅኑ ዝናብ መጥቷልና ወደየቤታችን እንግባ ከዚህም የምንጠጋበት ቤት ወይም ዋሻ የለምና አላቸው እረኞቹም ለኛ የማይታይ ለአንተ እንዴት ይታያል ብለው ተሳለቁባቸው፡፡
ቅዱስ ሀብተማርያምም የጥበብ አምላክ ልቡን በፀጋ መንፈስ ቅዱስ አበርትቶታልና እኔ የማውቀውን እናንተ አታውቁም ነገር ግን ወደየቤታችሁ ተመልሳችሁ በጊዜ ግቡ አሏቸው እነርሱም አንተ እራስህ ተመልሰህ ወደ ቤትህ ግባ እኛ ግን ፀሀይ ገና ቀትር እያለ ተመልሰን ወደ ቤታችን አንገባም አሉት፡፡ ይህንንም ባሉት ጊዜ በፍጥነት እየሮጠ በጎቹንም እያስሮጠ ወደ ቤቱ ገባ፡፡ ወደ ቤቱም ከገባ በኋላ ፅኑ ዝናብ መጣ ንፋስም ነፈሰ እነዛም አረኞች ይህ ሁሉ በላያቸው ላይ እየተፈፀመ ሳለም አልሸሹም ነበር፡፡ እግዚአብሄርም ክፋታቸውን አስቦባቸዋልና በላያቸው ላይ የጥፋት ውሀ አወረደባቸው ሁላቸውም ይህንን የጥፋት ውሀ እስኪፈፀምባቸው ድረስ አልተነቃነቁም ነበርና ሁሉም አለቁ፡፡
በዚህም ሌሊት ቃል ከሰማይ ሶስት ጊዜ ሀብተማርያም ሀብተማርያም ሲል ጠራው ይህም ህፃን አባቱ በአጠገቡ ተኝቶ ነበርና አባቱ የጠራው መስሎት አባቴ ሆይ አለሁ ሲል መለሰ፡፡ ይህንንም ማለቱ ቀድሞ በኤሊ ሊቀ ካህናት ጊዜ እንደተፈፀመ ሆኖበት ነው ሳሙ. 3÷3፡፡ እንደዚህም ሁሉ እግዚአብሔር ይህንን ህፃን ሀብተማርያም እያለ ሶስት ጊዜ ጠራው፡፡ ህፃኑም ሀብተማርያም ተነስቶ ታጥቆ እጅ ነስቶ እንደ ሳሙኤል ጌታዬ ባርያህ ይሰማል በል ተናገር አለው፡፡
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ከአሁን ጀምሮ ግን በግ ጠባቂዎች ከእርሻቸው ያልሆነውን ከሌላ እርሻ የሆነውን እሸት አምጥተው ብላ ቢሉህ አልበላም በላቸው፡፡ እናንተ ግን ብትወዱ ሄዳችሁ ብሉ በኋላ ግን ገሀነም ትገባላችሁ በእሳት ትቃጠላላችሁ በላቸው እንተን ግን ለሚሰሙ ለመረጥካቸው ቃሉን ትነግራቸው ዘንድ ከእኔ ጋር በሚስጢር ትነጋገር ዘንድ መርጬሃለሁ አለ፡፡ አቡነ ሀብተማርያምም ለቃልህ እታዘዝ ዘንድ እሺ ብያለሁ አለው የጠራውም ቃል ስሜንም በኋላ እነግርሃለሁ ነገር ግን የምልህን ቃልና ትዕዛዝ ጠብቅ አለው ዮሐ.
April 23, 2019
15÷10፡፡ ከጥቂት ቀን በኋላ ዳግመኛ በጎቹን እየጠበቀ ሳለ ብዙም የበጎች እረኞች አብረውት ሳሉ አንድ የበግ ጠባቂ መጥቶ የአቡነ ሀብተማርያምን በትር በጉልበቱ ነጥቆት ሄደ፡፡ አቡነ ሀብተማርያምም ተከትሎ ያን በግ ጠባቂ በትሬን ለምን ትቀማኛለህ ቢለው ያም በግ ጠባቂ በጉልበቴ ነጥቄሃለሁ አለው፡፡ አባታችን አቡነ ሀብተማርያምም በጎቼን የምጠንቅበት በትሬን እንዳትወስድብኝ በህያው እግዚአብሔር አምልሃለሁ ዳግመኛም አላምልህ
ም እቋቋምህም ዘንድ ሀይል የለኝምና አለው፡፡ ያም በግ ጠባቂ በትእቢት እንቢ አልኩህ አለው አቡነ ሀብተማርያምም ከእንግዲህ ወዲህ አምልህ ዘንድ አልደግምም ነገር ግን በአንተ ላይ የሚደረገውን ሀይልና ተዓምር አንተው ታያለህና ብሎ ዝም አለ፡፡ ያም በግ ጠባቂ በህዋው በተሰቀለ ጊዜ የእግዚአብሔር አገልጋይ ሀብተማርያም ሆይ ማረኝ እያለ ይጮህ ጀመር፡፡ ስመ እግዚአብሔርንና የፃድቁ ሀብተማርያምን ክብር ንቆ አቃሏልና ላዩ ታች ታቹ ላይ ቀኙ ግራው ግራው ቀኙ ሆኖ በአየር ተሰቅሎ ዋለ፡፡
በዚ የነበሩ የበግ ጠባቂዎችም ይህን ድንቅ ተአምር አይተው በጣም አደነቁ፡፡ እነርሱም አባታችን አቡነ ሀብተማርያምን ያደረጉትን ተአምር አይተዋልና እረኛውን እንዲምረው አሁንም አምላክን ስለወለደች ንዕድ ክብርት ስለምትሆን ስለ እመቤታችን ብለህ ማርልን አሉት ቅዱስ አባታችንም የሰቀልኩት እኔ ነኝን ነገር ግን በእግዚአብሔር ስም አማልኩት እንጂ የሃይሉንም ፅናት ያሳየው ዘንድ የሰቀለው እግዚአብሔር ነውና እርሱ ሁሉን ቻይና ይቅርባይ አምላክ ከተሰቀለበት ያውርደው አላቸው፡፡ አባታችንም ይህን ቃል በተናገረ ጊዜ የበግ ጠባቂው ከተሰቀለበት ወርዶ በእግሩ ቆመ በግ ጠባቂዎችም ወደ ሀገራቸው ተመልሰው ለዘመዶቻቸውና ለወገኖቻቸው ያዩትን ተአምር ከመጀመሪያው እስከመጨረሻው ተናገሩ፡፡ ይህንንም ተአምር የሀገሩ ሰዎች ሰምተው አደነቁ ይህ ታላቅ ፃድቅ ልጅ ነው በፊትም ቢሆን እግዚኦ መሀረነ ክርስቶስ እያለ ሲፀልይና እንደፈጣን ፈረስ ኮቴ ፍጥነት ሲሰግድ ፊቱንም በድንጋይ እየመታ የክርስቶስን ህማማት አስቦ ሲጋደል አይተነዋል ብለው መሰከሩ፡፡
፫ – ለአባታችን አቡነ ሀብተማርያም የተሰጣቸው ቃልኪዳኖች
አባታችን አቡነ ሀብተማርያም አራቱ ወንጌላት ከማንበብ ጋር ድካምና ተጋድሎ በበዛ ጊዜ ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል በቀኝና በግራ አስከትሎ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሲስ ክርስቶስ ወደ እርሱ መጥቶ በገሀድ ታየው ጌታችንም ወዳጅ ሀብተማርም ሆይ ሰላም ለአንተ ይሁን ባለው ጊዜ ከፈጣሪ ግርማ የተነሳ ደንግጦ ከመሬት ወደቀና እንደ በድን ሆነ ጌታችንም ክቡራት በሚሆኑ እጆቹ አንስቶ በፊቱ መንፈሰ ህይወትን አሳደረበት፡፡ ጌታችንም አቡነ ሀብተማርያምን ወዳጄ ሀብተማርያም ሆይ ድካምህና ገድልህ ሁሉ ለዘለዓለም መታሰቢያ ሊሆን በኢየሩሳሌም ሰማያዊት ተፅፎልሃል ብዬ በእውንት እነግርሀለሁ ለአንተ ለወደድኩህና ለመረጥኩህ ለወዳጄ የማትዮስንና የማርቆስን ወንጌል ባነበብክ ጊዜ ሁሉ ተጭነህ ወደ ምትሄድበት ቦታ ሁሉ የሚያደርስህ የብርሀን ሰረገላ እሰጥሀለሁ እንዳንተ ላሉ በዋሻ ከሚኖሩ ከመረጥኳቸው ቅዱሳን ትገናኝ ዘንድ ወደ ምስራቅ ወደ ምዕራብ ወደ ሰሜን ወደ ደቡብ ትሄድበት ዘንድ የብርሀን ሰረገላ ሰጥቼሀለሁ ከሰው ፊት ከተሰወሩ ባህታዊያን ጋር ኑር ዳግመኛ የሉቃስንና የዩሀንስን ወንጌል ባነበብክ ጊዜ በእነርሱ ተጭነህ ስጋዬን ደሜን ለመቅመስ ኢየሩሳሌም ትደርስ ዘንድ የእሳት ሰረገላ ሰጥቼሀለሁ፡፡ በፀሎትህ አምኖ በጎ ስራ ለሚሰራልህ ሁሉ በህይወት ሳለህ ልብስህን በመስጠት ወይም ምግብ ወይም እግር በማጠብ ወይም እንጨት ሣር በማቅረብ ወይም ውሀ በመቅዳት በመርዳት ለደከሙ ሁሉ እምርልሀለሁ ብዬ ቃልኪዳን ሰጥቼሀለሁ፡፡ በህይወቱ ሳለ ለሚሻ መልካሙን ስራ ሁሉ አደርግለታለሁ ከሞትም በኃላ መንግስተ ሰማያትን አወርሰዋለሁ በባለሟልነት እቀበላለሁ ከአንተ ጋርም ደስ እሰኘዋለሁ፡፡ አንተ ከሞትክም በኃላ ስምህን የጠራውንና ዝክርህን የዘከረውን ሁሉ የሀብተማርያም አምላክ ሆይ ከጠላት እጅ አድነኝ ያለኝን በህሊና ያሰበውን በልቦና የወሰነውን እፈፅምለታለሁ ሰውን ከቸነፈር ከተቅማጥ እኮእሳት መቃጠል መብረቅ በረሀብ ከሞት እንዲያድን እንደ ሀዋርያት ስልጣን ቃልኪዳን ተሰጠው፡፡ አንትን ገድልህን ቃልኪዳንህን የናቀውንና ያቃለለውን ሁሉ ፍፁም መበቀልን እበቀለዋለሁ፡፡ ወደ መከራ ቦታ አወርደዋለሁ በበጎ ሳይሆን በመዓት አይን እመለከተዋለሁ፡፡ ጠላቶችህን ይበቀልልህ ወዳጆችህን ይጠብቅልህ ዘንድ መልዕክተኛዬ ቅዱስ ሚካኤልም ዘወትር አይለይህ የሰጠሁህን ቃልኪዳን እንዳልነሳህ በራሴ ማልኩልህ፡፡ እንደ ወዳጄ እንደ ፈቅጦርም በእናቴ በድንግል ማርያም አተምኩህ፡፡ ፈቅጦርን ከሰማዕታት ሁሉ አብልጬ እንደወደድኩት አንተንም ከመነኮሳት ሁሉ አብልጬ ወድጄሀለሁና ይህ የሰጠሁህ ቃልኪዳኔ ለዘላለም ይሁንልህ አለው፡፡
በፃድቁ አባታችን በአቡነ ሀብተማርያም በቃል ኪዳናቸው ፀንተን እንድንገኝ የልዑል እግዚአብሔር ፈቃድ ይሁንልን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
በዚ የነበሩ የበግ ጠባቂዎችም ይህን ድንቅ ተአምር አይተው በጣም አደነቁ፡፡ እነርሱም አባታችን አቡነ ሀብተማርያምን ያደረጉትን ተአምር አይተዋልና እረኛውን እንዲምረው አሁንም አምላክን ስለወለደች ንዕድ ክብርት ስለምትሆን ስለ እመቤታችን ብለህ ማርልን አሉት ቅዱስ አባታችንም የሰቀልኩት እኔ ነኝን ነገር ግን በእግዚአብሔር ስም አማልኩት እንጂ የሃይሉንም ፅናት ያሳየው ዘንድ የሰቀለው እግዚአብሔር ነውና እርሱ ሁሉን ቻይና ይቅርባይ አምላክ ከተሰቀለበት ያውርደው አላቸው፡፡ አባታችንም ይህን ቃል በተናገረ ጊዜ የበግ ጠባቂው ከተሰቀለበት ወርዶ በእግሩ ቆመ በግ ጠባቂዎችም ወደ ሀገራቸው ተመልሰው ለዘመዶቻቸውና ለወገኖቻቸው ያዩትን ተአምር ከመጀመሪያው እስከመጨረሻው ተናገሩ፡፡ ይህንንም ተአምር የሀገሩ ሰዎች ሰምተው አደነቁ ይህ ታላቅ ፃድቅ ልጅ ነው በፊትም ቢሆን እግዚኦ መሀረነ ክርስቶስ እያለ ሲፀልይና እንደፈጣን ፈረስ ኮቴ ፍጥነት ሲሰግድ ፊቱንም በድንጋይ እየመታ የክርስቶስን ህማማት አስቦ ሲጋደል አይተነዋል ብለው መሰከሩ፡፡
፫ – ለአባታችን አቡነ ሀብተማርያም የተሰጣቸው ቃልኪዳኖች
አባታችን አቡነ ሀብተማርያም አራቱ ወንጌላት ከማንበብ ጋር ድካምና ተጋድሎ በበዛ ጊዜ ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል በቀኝና በግራ አስከትሎ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሲስ ክርስቶስ ወደ እርሱ መጥቶ በገሀድ ታየው ጌታችንም ወዳጅ ሀብተማርም ሆይ ሰላም ለአንተ ይሁን ባለው ጊዜ ከፈጣሪ ግርማ የተነሳ ደንግጦ ከመሬት ወደቀና እንደ በድን ሆነ ጌታችንም ክቡራት በሚሆኑ እጆቹ አንስቶ በፊቱ መንፈሰ ህይወትን አሳደረበት፡፡ ጌታችንም አቡነ ሀብተማርያምን ወዳጄ ሀብተማርያም ሆይ ድካምህና ገድልህ ሁሉ ለዘለዓለም መታሰቢያ ሊሆን በኢየሩሳሌም ሰማያዊት ተፅፎልሃል ብዬ በእውንት እነግርሀለሁ ለአንተ ለወደድኩህና ለመረጥኩህ ለወዳጄ የማትዮስንና የማርቆስን ወንጌል ባነበብክ ጊዜ ሁሉ ተጭነህ ወደ ምትሄድበት ቦታ ሁሉ የሚያደርስህ የብርሀን ሰረገላ እሰጥሀለሁ እንዳንተ ላሉ በዋሻ ከሚኖሩ ከመረጥኳቸው ቅዱሳን ትገናኝ ዘንድ ወደ ምስራቅ ወደ ምዕራብ ወደ ሰሜን ወደ ደቡብ ትሄድበት ዘንድ የብርሀን ሰረገላ ሰጥቼሀለሁ ከሰው ፊት ከተሰወሩ ባህታዊያን ጋር ኑር ዳግመኛ የሉቃስንና የዩሀንስን ወንጌል ባነበብክ ጊዜ በእነርሱ ተጭነህ ስጋዬን ደሜን ለመቅመስ ኢየሩሳሌም ትደርስ ዘንድ የእሳት ሰረገላ ሰጥቼሀለሁ፡፡ በፀሎትህ አምኖ በጎ ስራ ለሚሰራልህ ሁሉ በህይወት ሳለህ ልብስህን በመስጠት ወይም ምግብ ወይም እግር በማጠብ ወይም እንጨት ሣር በማቅረብ ወይም ውሀ በመቅዳት በመርዳት ለደከሙ ሁሉ እምርልሀለሁ ብዬ ቃልኪዳን ሰጥቼሀለሁ፡፡ በህይወቱ ሳለ ለሚሻ መልካሙን ስራ ሁሉ አደርግለታለሁ ከሞትም በኃላ መንግስተ ሰማያትን አወርሰዋለሁ በባለሟልነት እቀበላለሁ ከአንተ ጋርም ደስ እሰኘዋለሁ፡፡ አንተ ከሞትክም በኃላ ስምህን የጠራውንና ዝክርህን የዘከረውን ሁሉ የሀብተማርያም አምላክ ሆይ ከጠላት እጅ አድነኝ ያለኝን በህሊና ያሰበውን በልቦና የወሰነውን እፈፅምለታለሁ ሰውን ከቸነፈር ከተቅማጥ እኮእሳት መቃጠል መብረቅ በረሀብ ከሞት እንዲያድን እንደ ሀዋርያት ስልጣን ቃልኪዳን ተሰጠው፡፡ አንትን ገድልህን ቃልኪዳንህን የናቀውንና ያቃለለውን ሁሉ ፍፁም መበቀልን እበቀለዋለሁ፡፡ ወደ መከራ ቦታ አወርደዋለሁ በበጎ ሳይሆን በመዓት አይን እመለከተዋለሁ፡፡ ጠላቶችህን ይበቀልልህ ወዳጆችህን ይጠብቅልህ ዘንድ መልዕክተኛዬ ቅዱስ ሚካኤልም ዘወትር አይለይህ የሰጠሁህን ቃልኪዳን እንዳልነሳህ በራሴ ማልኩልህ፡፡ እንደ ወዳጄ እንደ ፈቅጦርም በእናቴ በድንግል ማርያም አተምኩህ፡፡ ፈቅጦርን ከሰማዕታት ሁሉ አብልጬ እንደወደድኩት አንተንም ከመነኮሳት ሁሉ አብልጬ ወድጄሀለሁና ይህ የሰጠሁህ ቃልኪዳኔ ለዘላለም ይሁንልህ አለው፡፡
በፃድቁ አባታችን በአቡነ ሀብተማርያም በቃል ኪዳናቸው ፀንተን እንድንገኝ የልዑል እግዚአብሔር ፈቃድ ይሁንልን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
🔔♥️🔔♥️🔔
ክርስቶስ ተንስአ እሙታን
ዐቢይ ኃይል ወስልጣን
አሰሮ ለሰይጣን
አግአዞ ለአዳም
ሰላም እምይእዜስ
ኮነ ፍሰሀ ወሰላም ::
“እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል።
ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል፥ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል።ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ፥ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋው አይጠፋበትም።"ማቴ 10:40-42
† እግዚአብሔር የቅዱሳንን ነፍስ ይጠብቃል ከሃጢአት እጅም ያድናቸዋል::† መዝ.96፡10
†♥️ † † እንኳን ለታላቁ ጸድቅ ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም ወርሃዊ መታሰቢያ በዓል በሰላም በጤና አደረሰ ን † † ♥️†
† † † በስመ እግዚአብሔር አብ እም ቅድመ ዓለም ዘሀሎ
ወበ ስመ እግዚአብሔር ወልድ ለስጋ ማርያም እንተ አልአሎ
ወበ ስመ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ እምኔሆሙ በኢሰስሎ
ኢየኃስድ ሰሌላዳ ስሙ ከመ እጽሐፍ ፊደሎ
ለዘ እም ኃበ አልቦ እሎንተ ዘአምጽአ ኩሎ::
† † † ሰላም ለጽንሰትከ እማህፀነ ቅድስት ዮስቴና
በብሥራተ ጻድቅ ባሕታዊ ሠናየ ዜና
ሐብተ ማርያም ጴጥሮስ ሐዋርያ ወልደ ዮና
መሐረኒ ምግባረ ጽድቅ ወጸግወኒ ልቦና
አፍቅሮ ቢጽ እኃሥሥ ዘምስለ ፍጽምት ትሕትና::
(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)
ረድኤት በረከቱ አይለየን ::♥️
@AbuneHabtemariyamtsdik
ክርስቶስ ተንስአ እሙታን
ዐቢይ ኃይል ወስልጣን
አሰሮ ለሰይጣን
አግአዞ ለአዳም
ሰላም እምይእዜስ
ኮነ ፍሰሀ ወሰላም ::
“እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል።
ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል፥ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል።ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ፥ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋው አይጠፋበትም።"ማቴ 10:40-42
† እግዚአብሔር የቅዱሳንን ነፍስ ይጠብቃል ከሃጢአት እጅም ያድናቸዋል::† መዝ.96፡10
†♥️ † † እንኳን ለታላቁ ጸድቅ ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም ወርሃዊ መታሰቢያ በዓል በሰላም በጤና አደረሰ ን † † ♥️†
† † † በስመ እግዚአብሔር አብ እም ቅድመ ዓለም ዘሀሎ
ወበ ስመ እግዚአብሔር ወልድ ለስጋ ማርያም እንተ አልአሎ
ወበ ስመ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ እምኔሆሙ በኢሰስሎ
ኢየኃስድ ሰሌላዳ ስሙ ከመ እጽሐፍ ፊደሎ
ለዘ እም ኃበ አልቦ እሎንተ ዘአምጽአ ኩሎ::
† † † ሰላም ለጽንሰትከ እማህፀነ ቅድስት ዮስቴና
በብሥራተ ጻድቅ ባሕታዊ ሠናየ ዜና
ሐብተ ማርያም ጴጥሮስ ሐዋርያ ወልደ ዮና
መሐረኒ ምግባረ ጽድቅ ወጸግወኒ ልቦና
አፍቅሮ ቢጽ እኃሥሥ ዘምስለ ፍጽምት ትሕትና::
(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)
ረድኤት በረከቱ አይለየን ::♥️
@AbuneHabtemariyamtsdik
May 3, 2019
ጻድቁ አቡነ ሀብተ ማርያም pinned «🔔♥️🔔♥️🔔 ክርስቶስ ተንስአ እሙታን ዐቢይ ኃይል ወስልጣን አሰሮ ለሰይጣን አግአዞ ለአዳም ሰላም እምይእዜስ ኮነ ፍሰሀ ወሰላም :: “እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል። ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል፥ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል።ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ፥…»
May 4, 2019
ጻድቁ አቡነ ሀብተ ማርያም pinned a video
May 10, 2019
✝️ክፍል ፩ – የትውልድ ታሪካቸው
የቅዱስ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም ትውልድ ሀገር የራውእይ የምትባል ምስራቃዊት ሀገር ውስጥ ሲሆን የኢትዮጵያ ንጉስ እስክንድር በነገሰ በሺ አራት መቶ ሰማንያ ስድስት ዓመተ ምህረት ፍሬ ብሩክ የሚባል አንድ ሰው በዚች ሀገር ውስጥ ነበር፡፡ ይኸውም ከከበሩም ሰዎች ተለይቶ ብዙ ገንዘብ ያለው ባለጸጋ ነበር፡፡ በህጋዊ ጋብቻ ስሟ ዮስቴና የምትባል ሴት አገባ ይህችውም ሴት በደግ ሥራ ሁሉ የተሸለመች ያጌጠች ነበረች፡፡ እነዲህ ባለ ሥራ ሳለች መንፈሳዊ ሀሳብ እንዲህ ሲል ተነሳባት ለአንቺ በዚህ ዓለም መኖር ምን ይረባሻል ዛሬ የሚያልፍ የሚጠፋ ነውና የሚመሰገንበት ለዘለዓለም የሚኖር የማያልፍ ሌላ ዓለም ይገለጣልና % ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌል “ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢገዛ ቢነዳ በነፍሱ ከተጎዳ ምን ይጠቅመዋል እንዳለ” ማቴ. 16÷26፣ ማር. 10÷36፡፡ ለአንቺ ግን በሰማይ ፀንቶ መኖርን ሁለተኛዋን ሀገር መያዝ ይሻላል የሚል ሀሳብ መጣባት፡፡ ይህን ካሰበች በኋላ ፈጥና ተነስታ በሌሊት ከቤት በመውጣት በሀገሯ አንፃር ትይዩ ወደ ሆነው ከጅቦች፣ ከነብሮች፣ ከዓሳማዎች፣ ከጦጦችና ከዝንጀሮዎች በስተቀር ምንም ምን ወደ ማይኖርበት በረሀ ደረሰች፡፡ በዚያም ደጃፏ ያልተዘጋ ትንሽ ዋሻ አገኘች፡፡ በዋሻው ውስጥም መዝሙረ ዳዊትን በአንክሮ የሚደግም ክቡር ባህታዊ አየች ባየችውም ጊዜ ደነገጠች እርሱም ሴቲቱን ባያት ጊዜ ፍርሀት መንቀጥቀጥ በላዩ ላይ ወረደበት፡፡ መጀመሪያ ስትገባ የጋኔን ምትሀት መስላው ነበርና ሰው መሆኗን ባወቀና በተረዳ ጊዜ ተቆጣት፡፡ እሷም ቤቴን ንብረቴን ያለኝን ሁሉ ትቼ መጥቻለሁ በዓለም ውስጥ ያለውን ሁሉ ንቄ እመንን ዘንድ እወዳለሁና ስለዚህም ወደዚህ ምድረበዳ መጣሁ አለችው፡፡ ይህም ባህታዊ በትህትናና በፈሪሀ እግዚአብሔር ይህን የሚያስደንቅ መልካም መልስ በመለሰችለት ጊዜ አንድ ሰዓት ያህል ካሰበ በኋላ ምንኩስናስ የለሽም ነገር ግን በፍቅር በአንድነት ወደ ቤትሽ ወደ ህጋዊ ባልሽ በሰላም ተመለሽ የተፈቀደልሽን እነግርሻለሁ ከህጋዊ ባለቤትሽ ወንድ ልጅን ትወልጃለሽ እርሱም ለዓለም ሁሉ የሚጠቅም ይሆናል የገድሉና የትሩፋቱ ዜና እስከ ዓለም ዳርቻ ይደርሳል በህይወተ ስጋ ሳለ በፈጣሪው እግዚአብሔር ፍቃድ የብዙዎችን ሰዎች ነፍሳት ከሲኦል ያወጣል እንደ መላእክትም ክንፈ ፀጋ ተሰጥቶታል፤ በሰው አካል ከስጋ ሆኖ ሳለ በተመስጦ ወደ ሰማይ የሥላሴን የአንድነትን የሦስትነትን ምስጢር ያያል አላት፡፡ ቅድስት ዮስቴናም ከአረጋዊ ባህታዊው ይህን ነገር ሰምታ አደነቀች የፈጣሪዬ ፈቃድ ከሆነ ወደ ቤቴ እመለሳለሁ አለች፡፡ ጥቂት ወራት ከቆየችም በኋላ መልኩ እንደ በረዶ ነጭ እንደ ፅጌረዳም ብሩህ ቀይ የሆነ መልከ መልካም ገፁ ብሩህ የሆነ ልጅ ወለደች ይህ ህፃን በግንቦት ወርህ በ26 ቀን በተወለደ ግዜ በአባቱና በእናቱ ቤት ታላቅ ደስታ ሆነ፡፡ ይህ ቅዱስ ህፃንም 40 ቀን በሞላው ጊዜ በኦሪትና በሉቃስ ወንጌል እንደተፃፈ በእግዚአብሔር ፊት ያቆሙት ዘንድ ወደ ካህን አቀረቡት፡፡ ክህኑም ለክርስትና አባቱ አሳልፎ ሰጠው ስሙንም ሀብተማርያም ብሎ ሰየመው ከዚህም በኋላ እናት አባቱም ተመለሱ፡፡ ይህ ቅዱስ ህፃን እግዚአብሔርን በመፍራት አደገ ከዕለታት አንድ ቀን ካህናቱ በቤተክርስቲያን ምህላ ሲያደርሱእግዚኦ መሀረነ ክርስቶስ እያሉ ሲፀልዩ ሰምቶ በልቡ ይህች ፀሎት በጣም ጥሩ መልካም ፀሎት ናት እኔ ይህችን ፀሎት መርጫታለሁ በዚህ ዓለም ከአሳች ህሊና በሚመጣውም ዓለም ከገሀነም እሳት እንድንድንባት አውቃለሁ አለ ስግደትንም እንደፈጣን ፈረስ ሩጫ ብዙ እስኪያልበው ድረስ ይሰግድ ነበር፡፡
====ይቆየን====
✔️ስለ #ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ #ሀብተ ማርያም ታሪክ ፣ ገድል ፣ ተአምራት እና መልክዕ እንዲያገኙ ይቀላቀሉ።
ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን የጻድቁ ቤተሰብ ይሁኑ
👇👇👇👇👇👇👇
@AbuneHabtemariyamtsdik
@AbuneHabtemariyamtsdik
👆👆👆👆👆👆👆👆
የቅዱስ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም ትውልድ ሀገር የራውእይ የምትባል ምስራቃዊት ሀገር ውስጥ ሲሆን የኢትዮጵያ ንጉስ እስክንድር በነገሰ በሺ አራት መቶ ሰማንያ ስድስት ዓመተ ምህረት ፍሬ ብሩክ የሚባል አንድ ሰው በዚች ሀገር ውስጥ ነበር፡፡ ይኸውም ከከበሩም ሰዎች ተለይቶ ብዙ ገንዘብ ያለው ባለጸጋ ነበር፡፡ በህጋዊ ጋብቻ ስሟ ዮስቴና የምትባል ሴት አገባ ይህችውም ሴት በደግ ሥራ ሁሉ የተሸለመች ያጌጠች ነበረች፡፡ እነዲህ ባለ ሥራ ሳለች መንፈሳዊ ሀሳብ እንዲህ ሲል ተነሳባት ለአንቺ በዚህ ዓለም መኖር ምን ይረባሻል ዛሬ የሚያልፍ የሚጠፋ ነውና የሚመሰገንበት ለዘለዓለም የሚኖር የማያልፍ ሌላ ዓለም ይገለጣልና % ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌል “ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢገዛ ቢነዳ በነፍሱ ከተጎዳ ምን ይጠቅመዋል እንዳለ” ማቴ. 16÷26፣ ማር. 10÷36፡፡ ለአንቺ ግን በሰማይ ፀንቶ መኖርን ሁለተኛዋን ሀገር መያዝ ይሻላል የሚል ሀሳብ መጣባት፡፡ ይህን ካሰበች በኋላ ፈጥና ተነስታ በሌሊት ከቤት በመውጣት በሀገሯ አንፃር ትይዩ ወደ ሆነው ከጅቦች፣ ከነብሮች፣ ከዓሳማዎች፣ ከጦጦችና ከዝንጀሮዎች በስተቀር ምንም ምን ወደ ማይኖርበት በረሀ ደረሰች፡፡ በዚያም ደጃፏ ያልተዘጋ ትንሽ ዋሻ አገኘች፡፡ በዋሻው ውስጥም መዝሙረ ዳዊትን በአንክሮ የሚደግም ክቡር ባህታዊ አየች ባየችውም ጊዜ ደነገጠች እርሱም ሴቲቱን ባያት ጊዜ ፍርሀት መንቀጥቀጥ በላዩ ላይ ወረደበት፡፡ መጀመሪያ ስትገባ የጋኔን ምትሀት መስላው ነበርና ሰው መሆኗን ባወቀና በተረዳ ጊዜ ተቆጣት፡፡ እሷም ቤቴን ንብረቴን ያለኝን ሁሉ ትቼ መጥቻለሁ በዓለም ውስጥ ያለውን ሁሉ ንቄ እመንን ዘንድ እወዳለሁና ስለዚህም ወደዚህ ምድረበዳ መጣሁ አለችው፡፡ ይህም ባህታዊ በትህትናና በፈሪሀ እግዚአብሔር ይህን የሚያስደንቅ መልካም መልስ በመለሰችለት ጊዜ አንድ ሰዓት ያህል ካሰበ በኋላ ምንኩስናስ የለሽም ነገር ግን በፍቅር በአንድነት ወደ ቤትሽ ወደ ህጋዊ ባልሽ በሰላም ተመለሽ የተፈቀደልሽን እነግርሻለሁ ከህጋዊ ባለቤትሽ ወንድ ልጅን ትወልጃለሽ እርሱም ለዓለም ሁሉ የሚጠቅም ይሆናል የገድሉና የትሩፋቱ ዜና እስከ ዓለም ዳርቻ ይደርሳል በህይወተ ስጋ ሳለ በፈጣሪው እግዚአብሔር ፍቃድ የብዙዎችን ሰዎች ነፍሳት ከሲኦል ያወጣል እንደ መላእክትም ክንፈ ፀጋ ተሰጥቶታል፤ በሰው አካል ከስጋ ሆኖ ሳለ በተመስጦ ወደ ሰማይ የሥላሴን የአንድነትን የሦስትነትን ምስጢር ያያል አላት፡፡ ቅድስት ዮስቴናም ከአረጋዊ ባህታዊው ይህን ነገር ሰምታ አደነቀች የፈጣሪዬ ፈቃድ ከሆነ ወደ ቤቴ እመለሳለሁ አለች፡፡ ጥቂት ወራት ከቆየችም በኋላ መልኩ እንደ በረዶ ነጭ እንደ ፅጌረዳም ብሩህ ቀይ የሆነ መልከ መልካም ገፁ ብሩህ የሆነ ልጅ ወለደች ይህ ህፃን በግንቦት ወርህ በ26 ቀን በተወለደ ግዜ በአባቱና በእናቱ ቤት ታላቅ ደስታ ሆነ፡፡ ይህ ቅዱስ ህፃንም 40 ቀን በሞላው ጊዜ በኦሪትና በሉቃስ ወንጌል እንደተፃፈ በእግዚአብሔር ፊት ያቆሙት ዘንድ ወደ ካህን አቀረቡት፡፡ ክህኑም ለክርስትና አባቱ አሳልፎ ሰጠው ስሙንም ሀብተማርያም ብሎ ሰየመው ከዚህም በኋላ እናት አባቱም ተመለሱ፡፡ ይህ ቅዱስ ህፃን እግዚአብሔርን በመፍራት አደገ ከዕለታት አንድ ቀን ካህናቱ በቤተክርስቲያን ምህላ ሲያደርሱእግዚኦ መሀረነ ክርስቶስ እያሉ ሲፀልዩ ሰምቶ በልቡ ይህች ፀሎት በጣም ጥሩ መልካም ፀሎት ናት እኔ ይህችን ፀሎት መርጫታለሁ በዚህ ዓለም ከአሳች ህሊና በሚመጣውም ዓለም ከገሀነም እሳት እንድንድንባት አውቃለሁ አለ ስግደትንም እንደፈጣን ፈረስ ሩጫ ብዙ እስኪያልበው ድረስ ይሰግድ ነበር፡፡
====ይቆየን====
✔️ስለ #ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ #ሀብተ ማርያም ታሪክ ፣ ገድል ፣ ተአምራት እና መልክዕ እንዲያገኙ ይቀላቀሉ።
ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን የጻድቁ ቤተሰብ ይሁኑ
👇👇👇👇👇👇👇
@AbuneHabtemariyamtsdik
@AbuneHabtemariyamtsdik
👆👆👆👆👆👆👆👆
May 12, 2019
ጻድቁ አቡነ ሀብተ ማርያም pinned «✝️ክፍል ፩ – የትውልድ ታሪካቸው የቅዱስ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም ትውልድ ሀገር የራውእይ የምትባል ምስራቃዊት ሀገር ውስጥ ሲሆን የኢትዮጵያ ንጉስ እስክንድር በነገሰ በሺ አራት መቶ ሰማንያ ስድስት ዓመተ ምህረት ፍሬ ብሩክ የሚባል አንድ ሰው በዚች ሀገር ውስጥ ነበር፡፡ ይኸውም ከከበሩም ሰዎች ተለይቶ ብዙ ገንዘብ ያለው ባለጸጋ ነበር፡፡ በህጋዊ ጋብቻ ስሟ ዮስቴና የምትባል ሴት አገባ ይህችውም…»
🤲ተአምራት
✝️ክፍል ፪ – አባታችን አቡነ ሀብተማርያም በሕይወት ሳሉ ካረፉም በኃላ ያደረጉት ተአምራት
አባታችን አቡነ ሀብተማርያም በሕይወት ሳሉም ሆነ ካረፉ በኋላ እጅግ ብዙ የሆኑ ተአምራትን አድርገዋል፡፡ ከነዚህ መካከልም በጥቂቱ እንመልከት፡፡ የአቡነ ሀብተማርም አባት ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያምን ከዕለታት በአንድ ቀን የበግ ጠባቂ አደረጓቸው፡፡ እግዚአብሔር ግን በኋላ ለብዙዎች ቅዱሳንና በዓለም ለሚኖሩ ምዕመናን በጎቹ ጠባቂ ያደርገው ዘንድ ወዶ መርጦታልና ያቀን እስኪደርስ ፈጣሪያችን ሀብትማርያምን ይጠብቀው ነበር በዚህም ዕለት በጎች ሲጠብቅ ብዙ የሚሆኑ የበጎች እረኞች እሸት ተሸክመው መጥተው ና እሸትን እንብላ አሏቸው፡፡ አባታችን አቡነ ሀብተምርያም ግን እኔስ አልበላም አሏቸው፡፡ እነርሱ እኛ ብላ ስንልህ ስለምን አትበላም አሉት አባትችንም ይህንን እሸት ከየት እንዳመጣችሁት ምንም እንደሆነ ስለማላውቅ ነው አላቸው (መጽሐፍ ኅጥእ ሰው እግዚአብሔርን የሚፈራውን ይንቀዋል ያቀልለዋል ብሎ እንደተናገረው) እረኞቹም አባታችንን በቁጣ ዓይን አዩዋቸው ብዙም ተቀጣጡባቸው ከዚህም በኋላ ከፊታቸው ተቀምጠው ያን ሰርቀው ያመጡትን እሸት መብላት ጀመሩ እሸቱንም በልተው ከጨረሱ በኋላ አባታችን ቅዱስ ሀብተማርያም በእነዚያን በግ ጠባቂዎችን የማንችለው ፅኑ ዝናብ መጥቷልና ወደየቤታችን እንግባ ከዚህም የምንጠጋበት ቤት ወይም ዋሻ የለምና አላቸው እረኞቹም ለኛ የማይታይ ለአንተ እንዴት ይታያል ብለው ተሳለቁባቸው፡፡
ቅዱስ ሀብተማርያምም የጥበብ አምላክ ልቡን በፀጋ መንፈስ ቅዱስ አበርትቶታልና እኔ የማውቀውን እናንተ አታውቁም ነገር ግን ወደየቤታችሁ ተመልሳችሁ በጊዜ ግቡ አሏቸው እነርሱም አንተ እራስህ ተመልሰህ ወደ ቤትህ ግባ እኛ ግን ፀሀይ ገና ቀትር እያለ ተመልሰን ወደ ቤታችን አንገባም አሉት፡፡ ይህንንም ባሉት ጊዜ በፍጥነት እየሮጠ በጎቹንም እያስሮጠ ወደ ቤቱ ገባ፡፡ ወደ ቤቱም ከገባ በኋላ ፅኑ ዝናብ መጣ ንፋስም ነፈሰ እነዛም አረኞች ይህ ሁሉ በላያቸው ላይ እየተፈፀመ ሳለም አልሸሹም ነበር፡፡ እግዚአብሄርም ክፋታቸውን አስቦባቸዋልና በላያቸው ላይ የጥፋት ውሀ አወረደባቸው ሁላቸውም ይህንን የጥፋት ውሀ እስኪፈፀምባቸው ድረስ አልተነቃነቁም ነበርና ሁሉም አለቁ፡፡
በዚህም ሌሊት ቃል ከሰማይ ሶስት ጊዜ ሀብተማርያም ሀብተማርያም ሲል ጠራው ይህም ህፃን አባቱ በአጠገቡ ተኝቶ ነበርና አባቱ የጠራው መስሎት አባቴ ሆይ አለሁ ሲል መለሰ፡፡ ይህንንም ማለቱ ቀድሞ በኤሊ ሊቀ ካህናት ጊዜ እንደተፈፀመ ሆኖበት ነው ሳሙ. 3÷3፡፡ እንደዚህም ሁሉ እግዚአብሔር ይህንን ህፃን ሀብተማርያም እያለ ሶስት ጊዜ ጠራው፡፡ ህፃኑም ሀብተማርያም ተነስቶ ታጥቆ እጅ ነስቶ እንደ ሳሙኤል ጌታዬ ባርያህ ይሰማል በል ተናገር አለው፡፡
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ከአሁን ጀምሮ ግን በግ ጠባቂዎች ከእርሻቸው ያልሆነውን ከሌላ እርሻ የሆነውን እሸት አምጥተው ብላ ቢሉህ አልበላም በላቸው፡፡ እናንተ ግን ብትወዱ ሄዳችሁ ብሉ በኋላ ግን ገሀነም ትገባላችሁ በእሳት ትቃጠላላችሁ በላቸው እንተን ግን ለሚሰሙ ለመረጥካቸው ቃሉን ትነግራቸው ዘንድ ከእኔ ጋር በሚስጢር ትነጋገር ዘንድ መርጬሃለሁ አለ፡፡ አቡነ ሀብተማርያምም ለቃልህ እታዘዝ ዘንድ እሺ ብያለሁ አለው የጠራውም ቃል ስሜንም በኋላ እነግርሃለሁ ነገር ግን የምልህን ቃልና ትዕዛዝ ጠብቅ አለው ዮሐ. 15÷10፡፡ ከጥቂት ቀን በኋላ ዳግመኛ በጎቹን እየጠበቀ ሳለ ብዙም የበጎች እረኞች አብረውት ሳሉ አንድ የበግ ጠባቂ መጥቶ የአቡነ ሀብተማርያምን በትር በጉልበቱ ነጥቆት ሄደ፡፡ አቡነ ሀብተማርያምም ተከትሎ ያን በግ ጠባቂ በትሬን ለምን ትቀማኛለህ ቢለው ያም በግ ጠባቂ በጉልበቴ ነጥቄሃለሁ አለው፡፡ አባታችን አቡነ ሀብተማርያምም በጎቼን የምጠንቅበት በትሬን እንዳትወስድብኝ በህያው እግዚአብሔር አምልሃለሁ ዳግመኛም አላምልህም እቋቋምህም ዘንድ ሀይል የለኝምና አለው፡፡ ያም በግ ጠባቂ በትእቢት እንቢ አልኩህ አለው አቡነ ሀብተማርያምም ከእንግዲህ ወዲህ አምልህ ዘንድ አልደግምም ነገር ግን በአንተ ላይ የሚደረገውን ሀይልና ተዓምር አንተው ታያለህና ብሎ ዝም አለ፡፡ ያም በግ ጠባቂ በህዋው በተሰቀለ ጊዜ የእግዚአብሔር አገልጋይ ሀብተማርያም ሆይ ማረኝ እያለ ይጮህ ጀመር፡፡ ስመ እግዚአብሔርንና የፃድቁ ሀብተማርያምን ክብር ንቆ አቃሏልና ላዩ ታች ታቹ ላይ ቀኙ ግራው ግራው ቀኙ ሆኖ በአየር ተሰቅሎ ዋለ፡፡
በዚ የነበሩ የበግ ጠባቂዎችም ይህን ድንቅ ተአምር አይተው በጣም አደነቁ፡፡ እነርሱም አባታችን አቡነ ሀብተማርያምን ያደረጉትን ተአምር አይተዋልና እረኛውን እንዲምረው አሁንም አምላክን ስለወለደች ንዕድ ክብርት ስለምትሆን ስለ እመቤታችን ብለህ ማርልን አሉት ቅዱስ አባታችንም የሰቀልኩት እኔ ነኝን ነገር ግን በእግዚአብሔር ስም አማልኩት እንጂ የሃይሉንም ፅናት ያሳየው ዘንድ የሰቀለው እግዚአብሔር ነውና እርሱ ሁሉን ቻይና ይቅርባይ አምላክ ከተሰቀለበት ያውርደው አላቸው፡፡ አባታችንም ይህን ቃል በተናገረ ጊዜ የበግ ጠባቂው ከተሰቀለበት ወርዶ በእግሩ ቆመ በግ ጠባቂዎችም ወደ ሀገራቸው ተመልሰው ለዘመዶቻቸውና ለወገኖቻቸው ያዩትን ተአምር ከመጀመሪያው እስከመጨረሻው ተናገሩ፡፡ ይህንንም ተአምር የሀገሩ ሰዎች ሰምተው አደነቁ ይህ ታላቅ ፃድቅ ልጅ ነው በፊትም ቢሆን እግዚኦ መሀረነ ክርስቶስ እያለ ሲፀልይና እንደፈጣን ፈረስ ኮቴ ፍጥነት ሲሰግድ ፊቱንም በድንጋይ እየመታ የክርስቶስን ህማማት አስቦ ሲጋደል አይተነዋል ብለው መሰከሩ፡፡
=====
🤲በፃድቁ አባታችን በአቡነ ሀብተማርያም በቃል ኪዳናቸው ፀንተን እንድንገኝ የልዑል እግዚአብሔር ፈቃድ ይሁንልን፡
✔️ስለ #ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ #ሀብተ ማርያም ታሪክ ፣ ገድል ፣ ተአምራት እና መልክዕ እንዲያገኙ ይቀላቀሉ።
ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን የጻድቁ ቤተሰብ ይሁኑ
👇👇👇👇👇👇👇
@AbuneHabtemariyamtsdik
@AbuneHabtemariyamtsdik
👆👆👆👆👆👆👆👆
✝️ክፍል ፪ – አባታችን አቡነ ሀብተማርያም በሕይወት ሳሉ ካረፉም በኃላ ያደረጉት ተአምራት
አባታችን አቡነ ሀብተማርያም በሕይወት ሳሉም ሆነ ካረፉ በኋላ እጅግ ብዙ የሆኑ ተአምራትን አድርገዋል፡፡ ከነዚህ መካከልም በጥቂቱ እንመልከት፡፡ የአቡነ ሀብተማርም አባት ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያምን ከዕለታት በአንድ ቀን የበግ ጠባቂ አደረጓቸው፡፡ እግዚአብሔር ግን በኋላ ለብዙዎች ቅዱሳንና በዓለም ለሚኖሩ ምዕመናን በጎቹ ጠባቂ ያደርገው ዘንድ ወዶ መርጦታልና ያቀን እስኪደርስ ፈጣሪያችን ሀብትማርያምን ይጠብቀው ነበር በዚህም ዕለት በጎች ሲጠብቅ ብዙ የሚሆኑ የበጎች እረኞች እሸት ተሸክመው መጥተው ና እሸትን እንብላ አሏቸው፡፡ አባታችን አቡነ ሀብተምርያም ግን እኔስ አልበላም አሏቸው፡፡ እነርሱ እኛ ብላ ስንልህ ስለምን አትበላም አሉት አባትችንም ይህንን እሸት ከየት እንዳመጣችሁት ምንም እንደሆነ ስለማላውቅ ነው አላቸው (መጽሐፍ ኅጥእ ሰው እግዚአብሔርን የሚፈራውን ይንቀዋል ያቀልለዋል ብሎ እንደተናገረው) እረኞቹም አባታችንን በቁጣ ዓይን አዩዋቸው ብዙም ተቀጣጡባቸው ከዚህም በኋላ ከፊታቸው ተቀምጠው ያን ሰርቀው ያመጡትን እሸት መብላት ጀመሩ እሸቱንም በልተው ከጨረሱ በኋላ አባታችን ቅዱስ ሀብተማርያም በእነዚያን በግ ጠባቂዎችን የማንችለው ፅኑ ዝናብ መጥቷልና ወደየቤታችን እንግባ ከዚህም የምንጠጋበት ቤት ወይም ዋሻ የለምና አላቸው እረኞቹም ለኛ የማይታይ ለአንተ እንዴት ይታያል ብለው ተሳለቁባቸው፡፡
ቅዱስ ሀብተማርያምም የጥበብ አምላክ ልቡን በፀጋ መንፈስ ቅዱስ አበርትቶታልና እኔ የማውቀውን እናንተ አታውቁም ነገር ግን ወደየቤታችሁ ተመልሳችሁ በጊዜ ግቡ አሏቸው እነርሱም አንተ እራስህ ተመልሰህ ወደ ቤትህ ግባ እኛ ግን ፀሀይ ገና ቀትር እያለ ተመልሰን ወደ ቤታችን አንገባም አሉት፡፡ ይህንንም ባሉት ጊዜ በፍጥነት እየሮጠ በጎቹንም እያስሮጠ ወደ ቤቱ ገባ፡፡ ወደ ቤቱም ከገባ በኋላ ፅኑ ዝናብ መጣ ንፋስም ነፈሰ እነዛም አረኞች ይህ ሁሉ በላያቸው ላይ እየተፈፀመ ሳለም አልሸሹም ነበር፡፡ እግዚአብሄርም ክፋታቸውን አስቦባቸዋልና በላያቸው ላይ የጥፋት ውሀ አወረደባቸው ሁላቸውም ይህንን የጥፋት ውሀ እስኪፈፀምባቸው ድረስ አልተነቃነቁም ነበርና ሁሉም አለቁ፡፡
በዚህም ሌሊት ቃል ከሰማይ ሶስት ጊዜ ሀብተማርያም ሀብተማርያም ሲል ጠራው ይህም ህፃን አባቱ በአጠገቡ ተኝቶ ነበርና አባቱ የጠራው መስሎት አባቴ ሆይ አለሁ ሲል መለሰ፡፡ ይህንንም ማለቱ ቀድሞ በኤሊ ሊቀ ካህናት ጊዜ እንደተፈፀመ ሆኖበት ነው ሳሙ. 3÷3፡፡ እንደዚህም ሁሉ እግዚአብሔር ይህንን ህፃን ሀብተማርያም እያለ ሶስት ጊዜ ጠራው፡፡ ህፃኑም ሀብተማርያም ተነስቶ ታጥቆ እጅ ነስቶ እንደ ሳሙኤል ጌታዬ ባርያህ ይሰማል በል ተናገር አለው፡፡
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ከአሁን ጀምሮ ግን በግ ጠባቂዎች ከእርሻቸው ያልሆነውን ከሌላ እርሻ የሆነውን እሸት አምጥተው ብላ ቢሉህ አልበላም በላቸው፡፡ እናንተ ግን ብትወዱ ሄዳችሁ ብሉ በኋላ ግን ገሀነም ትገባላችሁ በእሳት ትቃጠላላችሁ በላቸው እንተን ግን ለሚሰሙ ለመረጥካቸው ቃሉን ትነግራቸው ዘንድ ከእኔ ጋር በሚስጢር ትነጋገር ዘንድ መርጬሃለሁ አለ፡፡ አቡነ ሀብተማርያምም ለቃልህ እታዘዝ ዘንድ እሺ ብያለሁ አለው የጠራውም ቃል ስሜንም በኋላ እነግርሃለሁ ነገር ግን የምልህን ቃልና ትዕዛዝ ጠብቅ አለው ዮሐ. 15÷10፡፡ ከጥቂት ቀን በኋላ ዳግመኛ በጎቹን እየጠበቀ ሳለ ብዙም የበጎች እረኞች አብረውት ሳሉ አንድ የበግ ጠባቂ መጥቶ የአቡነ ሀብተማርያምን በትር በጉልበቱ ነጥቆት ሄደ፡፡ አቡነ ሀብተማርያምም ተከትሎ ያን በግ ጠባቂ በትሬን ለምን ትቀማኛለህ ቢለው ያም በግ ጠባቂ በጉልበቴ ነጥቄሃለሁ አለው፡፡ አባታችን አቡነ ሀብተማርያምም በጎቼን የምጠንቅበት በትሬን እንዳትወስድብኝ በህያው እግዚአብሔር አምልሃለሁ ዳግመኛም አላምልህም እቋቋምህም ዘንድ ሀይል የለኝምና አለው፡፡ ያም በግ ጠባቂ በትእቢት እንቢ አልኩህ አለው አቡነ ሀብተማርያምም ከእንግዲህ ወዲህ አምልህ ዘንድ አልደግምም ነገር ግን በአንተ ላይ የሚደረገውን ሀይልና ተዓምር አንተው ታያለህና ብሎ ዝም አለ፡፡ ያም በግ ጠባቂ በህዋው በተሰቀለ ጊዜ የእግዚአብሔር አገልጋይ ሀብተማርያም ሆይ ማረኝ እያለ ይጮህ ጀመር፡፡ ስመ እግዚአብሔርንና የፃድቁ ሀብተማርያምን ክብር ንቆ አቃሏልና ላዩ ታች ታቹ ላይ ቀኙ ግራው ግራው ቀኙ ሆኖ በአየር ተሰቅሎ ዋለ፡፡
በዚ የነበሩ የበግ ጠባቂዎችም ይህን ድንቅ ተአምር አይተው በጣም አደነቁ፡፡ እነርሱም አባታችን አቡነ ሀብተማርያምን ያደረጉትን ተአምር አይተዋልና እረኛውን እንዲምረው አሁንም አምላክን ስለወለደች ንዕድ ክብርት ስለምትሆን ስለ እመቤታችን ብለህ ማርልን አሉት ቅዱስ አባታችንም የሰቀልኩት እኔ ነኝን ነገር ግን በእግዚአብሔር ስም አማልኩት እንጂ የሃይሉንም ፅናት ያሳየው ዘንድ የሰቀለው እግዚአብሔር ነውና እርሱ ሁሉን ቻይና ይቅርባይ አምላክ ከተሰቀለበት ያውርደው አላቸው፡፡ አባታችንም ይህን ቃል በተናገረ ጊዜ የበግ ጠባቂው ከተሰቀለበት ወርዶ በእግሩ ቆመ በግ ጠባቂዎችም ወደ ሀገራቸው ተመልሰው ለዘመዶቻቸውና ለወገኖቻቸው ያዩትን ተአምር ከመጀመሪያው እስከመጨረሻው ተናገሩ፡፡ ይህንንም ተአምር የሀገሩ ሰዎች ሰምተው አደነቁ ይህ ታላቅ ፃድቅ ልጅ ነው በፊትም ቢሆን እግዚኦ መሀረነ ክርስቶስ እያለ ሲፀልይና እንደፈጣን ፈረስ ኮቴ ፍጥነት ሲሰግድ ፊቱንም በድንጋይ እየመታ የክርስቶስን ህማማት አስቦ ሲጋደል አይተነዋል ብለው መሰከሩ፡፡
=====
🤲በፃድቁ አባታችን በአቡነ ሀብተማርያም በቃል ኪዳናቸው ፀንተን እንድንገኝ የልዑል እግዚአብሔር ፈቃድ ይሁንልን፡
✔️ስለ #ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ #ሀብተ ማርያም ታሪክ ፣ ገድል ፣ ተአምራት እና መልክዕ እንዲያገኙ ይቀላቀሉ።
ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን የጻድቁ ቤተሰብ ይሁኑ
👇👇👇👇👇👇👇
@AbuneHabtemariyamtsdik
@AbuneHabtemariyamtsdik
👆👆👆👆👆👆👆👆
May 15, 2019
ጻድቁ አቡነ ሀብተ ማርያም pinned «🤲ተአምራት ✝️ክፍል ፪ – አባታችን አቡነ ሀብተማርያም በሕይወት ሳሉ ካረፉም በኃላ ያደረጉት ተአምራት አባታችን አቡነ ሀብተማርያም በሕይወት ሳሉም ሆነ ካረፉ በኋላ እጅግ ብዙ የሆኑ ተአምራትን አድርገዋል፡፡ ከነዚህ መካከልም በጥቂቱ እንመልከት፡፡ የአቡነ ሀብተማርም አባት ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያምን ከዕለታት በአንድ ቀን የበግ ጠባቂ አደረጓቸው፡፡ እግዚአብሔር ግን በኋላ ለብዙዎች ቅዱሳንና በዓለም ለሚኖሩ…»
🌿ቃልኪዳናቸው ✝️ክፍል ፫ – ለአባታችን አቡነ ሀብተማርያም የተሰጣቸው ቃልኪዳኖች
አባታችን አቡነ ሀብተማርያም አራቱ ወንጌላት ከማንበብ ጋር ድካምና ተጋድሎ በበዛ ጊዜ ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል በቀኝና በግራ አስከትሎ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሲስ ክርስቶስ ወደ እርሱ መጥቶ በገሀድ ታየው ጌታችንም ወዳጅ ሀብተማርም ሆይ ሰላም ለአንተ ይሁን ባለው ጊዜ ከፈጣሪ ግርማ የተነሳ ደንግጦ ከመሬት ወደቀና እንደ በድን ሆነ ጌታችንም ክቡራት በሚሆኑ እጆቹ አንስቶ በፊቱ መንፈሰ ህይወትን አሳደረበት፡፡ ጌታችንም አቡነ ሀብተማርያምን ወዳጄ ሀብተማርያም ሆይ ድካምህና ገድልህ ሁሉ ለዘለዓለም መታሰቢያ ሊሆን በኢየሩሳሌም ሰማያዊት ተፅፎልሃል ብዬ በእውንት እነግርሀለሁ ለአንተ ለወደድኩህና ለመረጥኩህ ለወዳጄ የማትዮስንና የማርቆስን ወንጌል ባነበብክ ጊዜ ሁሉ ተጭነህ ወደ ምትሄድበት ቦታ ሁሉ የሚያደርስህ የብርሀን ሰረገላ እሰጥሀለሁ እንዳንተ ላሉ በዋሻ ከሚኖሩ ከመረጥኳቸው ቅዱሳን ትገናኝ ዘንድ ወደ ምስራቅ ወደ ምዕራብ ወደ ሰሜን ወደ ደቡብ ትሄድበት ዘንድ የብርሀን ሰረገላ ሰጥቼሀለሁ ከሰው ፊት ከተሰወሩ ባህታዊያን ጋር ኑር ዳግመኛ የሉቃስንና የዩሀንስን ወንጌል ባነበብክ ጊዜ በእነርሱ ተጭነህ ስጋዬን ደሜን ለመቅመስ ኢየሩሳሌም ትደርስ ዘንድ የእሳት ሰረገላ ሰጥቼሀለሁ፡፡
#በፀሎትህ አምኖ በጎ ስራ ለሚሰራልህ ሁሉ በህይወት ሳለህ ልብስህን በመስጠት ወይም ምግብ ወይም እግር በማጠብ ወይም እንጨት ሣር በማቅረብ ወይም ውሀ በመቅዳት በመርዳት ለደከሙ ሁሉ እምርልሀለሁ ብዬ ቃልኪዳን ሰጥቼሀለሁ፡፡ በህይወቱ ሳለ ለሚሻ መልካሙን ስራ ሁሉ አደርግለታለሁ ከሞትም በኃላ መንግስተ ሰማያትን አወርሰዋለሁ በባለሟልነት እቀበላለሁ ከአንተ ጋርም ደስ እሰኘዋለሁ፡፡ #አንተ ከሞትክም በኃላ ስምህን የጠራውንና ዝክርህን የዘከረውን ሁሉ የሀብተማርያም አምላክ ሆይ ከጠላት እጅ አድነኝ ያለኝን በህሊና ያሰበውን በልቦና የወሰነውን እፈፅምለታለሁ
#ሰውን ከቸነፈር ከተቅማጥ እኮእሳት መቃጠል መብረቅ በረሀብ ከሞት እንዲያድን እንደ ሀዋርያት ስልጣን ቃልኪዳን ተሰጠው፡፡
#የ አንትን ገድልህን ቃልኪዳንህን የናቀውንና ያቃለለውን ሁሉ ፍፁም መበቀልን እበቀለዋለሁ፡፡ ወደ መከራ ቦታ አወርደዋለሁ በበጎ ሳይሆን በመዓት አይን እመለከተዋለሁ፡፡ ጠላቶችህን ይበቀልልህ ወዳጆችህን ይጠብቅልህ ዘንድ መልዕክተኛዬ ቅዱስ ሚካኤልም ዘወትር አይለይህ
😇የሰጠሁህን ቃልኪዳን እንዳልነሳህ በራሴ ማልኩልህ፡፡ እንደ ወዳጄ እንደ ፈቅጦርም በእናቴ በድንግል ማርያም አተምኩህ፡፡
😇ፈቅጦርን ከሰማዕታት ሁሉ አብልጬ እንደወደድኩት አንተንም ከመነኮሳት ሁሉ አብልጬ ወድጄሀለሁና ይህ የሰጠሁህ ቃልኪዳኔ ለዘላለም ይሁንልህ አለው፡፡
🤲በፃድቁ አባታችን በአቡነ ሀብተማርያም በቃል ኪዳናቸው ፀንተን እንድንገኝ የልዑል እግዚአብሔር ፈቃድ ይሁንልን፡፡🤲
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
✔️ስለ #ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ #ሀብተ ማርያም ታሪክ ፣ ገድል ፣ ተአምራት እና መልክዕ እንዲያገኙ ይቀላቀሉ።
ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን የጻድቁ ቤተሰብ ይሁኑ
👇👇👇👇👇👇👇
@AbuneHabtemariyamtsdik
@AbuneHabtemariyamtsdik
👆👆👆👆👆👆👆👆
አባታችን አቡነ ሀብተማርያም አራቱ ወንጌላት ከማንበብ ጋር ድካምና ተጋድሎ በበዛ ጊዜ ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል በቀኝና በግራ አስከትሎ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሲስ ክርስቶስ ወደ እርሱ መጥቶ በገሀድ ታየው ጌታችንም ወዳጅ ሀብተማርም ሆይ ሰላም ለአንተ ይሁን ባለው ጊዜ ከፈጣሪ ግርማ የተነሳ ደንግጦ ከመሬት ወደቀና እንደ በድን ሆነ ጌታችንም ክቡራት በሚሆኑ እጆቹ አንስቶ በፊቱ መንፈሰ ህይወትን አሳደረበት፡፡ ጌታችንም አቡነ ሀብተማርያምን ወዳጄ ሀብተማርያም ሆይ ድካምህና ገድልህ ሁሉ ለዘለዓለም መታሰቢያ ሊሆን በኢየሩሳሌም ሰማያዊት ተፅፎልሃል ብዬ በእውንት እነግርሀለሁ ለአንተ ለወደድኩህና ለመረጥኩህ ለወዳጄ የማትዮስንና የማርቆስን ወንጌል ባነበብክ ጊዜ ሁሉ ተጭነህ ወደ ምትሄድበት ቦታ ሁሉ የሚያደርስህ የብርሀን ሰረገላ እሰጥሀለሁ እንዳንተ ላሉ በዋሻ ከሚኖሩ ከመረጥኳቸው ቅዱሳን ትገናኝ ዘንድ ወደ ምስራቅ ወደ ምዕራብ ወደ ሰሜን ወደ ደቡብ ትሄድበት ዘንድ የብርሀን ሰረገላ ሰጥቼሀለሁ ከሰው ፊት ከተሰወሩ ባህታዊያን ጋር ኑር ዳግመኛ የሉቃስንና የዩሀንስን ወንጌል ባነበብክ ጊዜ በእነርሱ ተጭነህ ስጋዬን ደሜን ለመቅመስ ኢየሩሳሌም ትደርስ ዘንድ የእሳት ሰረገላ ሰጥቼሀለሁ፡፡
#በፀሎትህ አምኖ በጎ ስራ ለሚሰራልህ ሁሉ በህይወት ሳለህ ልብስህን በመስጠት ወይም ምግብ ወይም እግር በማጠብ ወይም እንጨት ሣር በማቅረብ ወይም ውሀ በመቅዳት በመርዳት ለደከሙ ሁሉ እምርልሀለሁ ብዬ ቃልኪዳን ሰጥቼሀለሁ፡፡ በህይወቱ ሳለ ለሚሻ መልካሙን ስራ ሁሉ አደርግለታለሁ ከሞትም በኃላ መንግስተ ሰማያትን አወርሰዋለሁ በባለሟልነት እቀበላለሁ ከአንተ ጋርም ደስ እሰኘዋለሁ፡፡ #አንተ ከሞትክም በኃላ ስምህን የጠራውንና ዝክርህን የዘከረውን ሁሉ የሀብተማርያም አምላክ ሆይ ከጠላት እጅ አድነኝ ያለኝን በህሊና ያሰበውን በልቦና የወሰነውን እፈፅምለታለሁ
#ሰውን ከቸነፈር ከተቅማጥ እኮእሳት መቃጠል መብረቅ በረሀብ ከሞት እንዲያድን እንደ ሀዋርያት ስልጣን ቃልኪዳን ተሰጠው፡፡
#የ አንትን ገድልህን ቃልኪዳንህን የናቀውንና ያቃለለውን ሁሉ ፍፁም መበቀልን እበቀለዋለሁ፡፡ ወደ መከራ ቦታ አወርደዋለሁ በበጎ ሳይሆን በመዓት አይን እመለከተዋለሁ፡፡ ጠላቶችህን ይበቀልልህ ወዳጆችህን ይጠብቅልህ ዘንድ መልዕክተኛዬ ቅዱስ ሚካኤልም ዘወትር አይለይህ
😇የሰጠሁህን ቃልኪዳን እንዳልነሳህ በራሴ ማልኩልህ፡፡ እንደ ወዳጄ እንደ ፈቅጦርም በእናቴ በድንግል ማርያም አተምኩህ፡፡
😇ፈቅጦርን ከሰማዕታት ሁሉ አብልጬ እንደወደድኩት አንተንም ከመነኮሳት ሁሉ አብልጬ ወድጄሀለሁና ይህ የሰጠሁህ ቃልኪዳኔ ለዘላለም ይሁንልህ አለው፡፡
🤲በፃድቁ አባታችን በአቡነ ሀብተማርያም በቃል ኪዳናቸው ፀንተን እንድንገኝ የልዑል እግዚአብሔር ፈቃድ ይሁንልን፡፡🤲
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
✔️ስለ #ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ #ሀብተ ማርያም ታሪክ ፣ ገድል ፣ ተአምራት እና መልክዕ እንዲያገኙ ይቀላቀሉ።
ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን የጻድቁ ቤተሰብ ይሁኑ
👇👇👇👇👇👇👇
@AbuneHabtemariyamtsdik
@AbuneHabtemariyamtsdik
👆👆👆👆👆👆👆👆
May 17, 2019
May 26, 2019
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM✝️🔔ግንቦት 26 ልደቱ ለ አቡነ ሀብተማርያም🔔✝️
†† † ❤️እንኳን ለታላቁ ጸድቅ ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም የልደት መታሰቢያ በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደሰችሁ† † †❤️
† † “እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል። ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል፥ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል።ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ፥ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋው አይጠፋበትም።" † † ማቴ 10:40
† † † ሰላም ለልደትከ እማህፀነ ቅድስት ዮስቴና
በብሥራተ ጻድቅ ባሕታዊ ሠናየ ዜና
ሐብተ ማርያም ጴጥሮስ ሐዋርያ ወልደ ዮና
መሐረኒ ምግባረ ጽድቅ ወጸግወኒ ልቦና
አፍቅሮ ቢጽ እኃሥሥ ዘምስለ ፍጽምት ትሕትና::
(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)
ረድኤት በረከቱ አይለየን ::😇🤲😇
👇👇👇👇👇👇👇
@AbuneHabtemariyamtsdi
†† † ❤️እንኳን ለታላቁ ጸድቅ ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም የልደት መታሰቢያ በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደሰችሁ† † †❤️
† † “እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል። ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል፥ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል።ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ፥ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋው አይጠፋበትም።" † † ማቴ 10:40
† † † ሰላም ለልደትከ እማህፀነ ቅድስት ዮስቴና
በብሥራተ ጻድቅ ባሕታዊ ሠናየ ዜና
ሐብተ ማርያም ጴጥሮስ ሐዋርያ ወልደ ዮና
መሐረኒ ምግባረ ጽድቅ ወጸግወኒ ልቦና
አፍቅሮ ቢጽ እኃሥሥ ዘምስለ ፍጽምት ትሕትና::
(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)
ረድኤት በረከቱ አይለየን ::😇🤲😇
👇👇👇👇👇👇👇
@AbuneHabtemariyamtsdi
June 2, 2019
June 5, 2019
ጻድቁ አቡነ ሀብተ ማርያም pinned a video
June 10, 2019
June 12, 2019
† እግዚአብሔር የቅዱሳንን ነፍስ ይጠብቃል ከሃጢአት እጅም ያድናቸዋል::† መዝ.96፡10
† † † ሰላም ለአራኅከ ነሣኤ ኅለት ዘአሚን::
ዘይትባሕዩ ቦቱ አባግዒከ ዝርዋን::
ሀብተ ማርያም መርስ ሀብተ ማርያም ዛኅን::
ይሱቀኒ እምትንታኔ ጸሎትከ በትረ ሐፂን::
ለቁረተ ነፍስየ ካዕበ ቃልከ ክዳን::
† † † በአለም የተበተኑ በጏች የተባሉ ልጆችህ የሚጠበቅበት የእምነት ዘንግን ለጨበጠ መሐል እጅህ ሰላምታ ይገባል::
ጻድቁ አባቴ ሀብተማርያም ሆይ የዚች አለም ጸጥታዋና ሰላሟ አንተ ነህ እኮ እኔን ለመውደቅ የተፍገመገምኩትን እንደብረት ዘንግ የሆነ ጸሎትህ ከወደቅኩበት መሬት ያንሳኝ ይደግፈኝ ሁለተኛም የጏሰቆለች ነፍሴን ቃልኪዳንህ አይለያት::
(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)❤️
† † † ሰላም ለአራኅከ ነሣኤ ኅለት ዘአሚን::
ዘይትባሕዩ ቦቱ አባግዒከ ዝርዋን::
ሀብተ ማርያም መርስ ሀብተ ማርያም ዛኅን::
ይሱቀኒ እምትንታኔ ጸሎትከ በትረ ሐፂን::
ለቁረተ ነፍስየ ካዕበ ቃልከ ክዳን::
† † † በአለም የተበተኑ በጏች የተባሉ ልጆችህ የሚጠበቅበት የእምነት ዘንግን ለጨበጠ መሐል እጅህ ሰላምታ ይገባል::
ጻድቁ አባቴ ሀብተማርያም ሆይ የዚች አለም ጸጥታዋና ሰላሟ አንተ ነህ እኮ እኔን ለመውደቅ የተፍገመገምኩትን እንደብረት ዘንግ የሆነ ጸሎትህ ከወደቅኩበት መሬት ያንሳኝ ይደግፈኝ ሁለተኛም የጏሰቆለች ነፍሴን ቃልኪዳንህ አይለያት::
(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)❤️
June 13, 2019
July 2, 2019
† † እግዚአብሔር የቅዱሳንን ነፍስ ይጠብቃል ከሃጢአት እጅም ያድናቸዋል::† መዝ.96፡10
✝️† እንኳን ለታላቁ ጸድቅ ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም በዓል በሰላም በጤና አደረሰ ን †✝️
አምላከ ሀብተ ማርያም ማረን
የጻድቁ ሀብተ ማርያም ረድኤት በረከት ይደርብን በቃልኪዳናቸው ይጠብቁን 🤲🤲🤲
መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያምን ያድምጡ👇👇👇👇
https://myvideo.cc/movies/aU9xdy95VXU4Q1ZWMzNpc0ltenZNd2ZMMkI2TkdKdEJmQ2lUMENEZzNZUT0
✝️† እንኳን ለታላቁ ጸድቅ ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም በዓል በሰላም በጤና አደረሰ ን †✝️
አምላከ ሀብተ ማርያም ማረን
የጻድቁ ሀብተ ማርያም ረድኤት በረከት ይደርብን በቃልኪዳናቸው ይጠብቁን 🤲🤲🤲
መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያምን ያድምጡ👇👇👇👇
https://myvideo.cc/movies/aU9xdy95VXU4Q1ZWMzNpc0ltenZNd2ZMMkI2TkdKdEJmQ2lUMENEZzNZUT0
myvideo.cc
Best movies in good quality | Quick Video Search | New Movies Online — MyVideo
Best movies in good quality | Quick Video Search | New Movies Online...
August 1, 2019
ጻድቁ አቡነ ሀብተ ማርያም pinned «🌿ቃልኪዳናቸው ✝️ክፍል ፫ – ለአባታችን አቡነ ሀብተማርያም የተሰጣቸው ቃልኪዳኖች አባታችን አቡነ ሀብተማርያም አራቱ ወንጌላት ከማንበብ ጋር ድካምና ተጋድሎ በበዛ ጊዜ ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል በቀኝና በግራ አስከትሎ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሲስ ክርስቶስ ወደ እርሱ መጥቶ በገሀድ ታየው ጌታችንም ወዳጅ ሀብተማርም ሆይ ሰላም ለአንተ ይሁን ባለው ጊዜ ከፈጣሪ ግርማ የተነሳ ደንግጦ ከመሬት ወደቀና እንደ…»
August 16, 2019
🕊🔔‹‹ጸልዩ በእንተ ሰላመ ቤተክርስቲያን
አሐቲ ቅድስት ጉባዔ እንተ ሐዋርያት ርትዕት በኀበ እግዚአብሔር››
🕊††እንኳን ለታላቁ ጸድቅ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደረሳችሁ🕊
✝️🕊ነሐሴ 26 ፅንሰቱ ለ አቡነ ሀብተማርያም
† † † ሰላም ለፅንሰትከ እማህፀነ ቅድስት ዮስቴና
በብሥራተ ጻድቅ ባሕታዊ ሠናየ ዜና
ሐብተ ማርያም ጴጥሮስ ሐዋርያ ወልደ ዮና
መሐረኒ ምግባረ ጽድቅ ወጸግወኒ ልቦና
አፍቅሮ ቢጽ እኃሥሥ ዘምስለ ፍጽምት
ትሕትና::
(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)
🌹እሰይ ተፀነሱ በዛሬው ዕለት
አቡነ ሀብተማርያም ታላቁ አባት
የምስራች እልል በሉ የ አዳም ልጆችን ሁሉ የምስራች እልል በሉ ክርስቲያኖች ሁሉ🌹
😇ብዙ ልጆች አሉት ለስሙ ምስክር
በዙሪያው ያሉትን አብቅቶል ለክብር
ስለ ፍፁም ምልጃው ለኔ ግን ይለያል
ፃድቁ አባቴ ስለው ደስ ይለኛል😇
ረድኤት በረከቱ አይለየን ::😇🤲😇
👇👇👇👇👇👇👇
@AbuneHabtemariyamtsdik
አሐቲ ቅድስት ጉባዔ እንተ ሐዋርያት ርትዕት በኀበ እግዚአብሔር››
🕊††እንኳን ለታላቁ ጸድቅ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደረሳችሁ🕊
✝️🕊ነሐሴ 26 ፅንሰቱ ለ አቡነ ሀብተማርያም
† † † ሰላም ለፅንሰትከ እማህፀነ ቅድስት ዮስቴና
በብሥራተ ጻድቅ ባሕታዊ ሠናየ ዜና
ሐብተ ማርያም ጴጥሮስ ሐዋርያ ወልደ ዮና
መሐረኒ ምግባረ ጽድቅ ወጸግወኒ ልቦና
አፍቅሮ ቢጽ እኃሥሥ ዘምስለ ፍጽምት
ትሕትና::
(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)
🌹እሰይ ተፀነሱ በዛሬው ዕለት
አቡነ ሀብተማርያም ታላቁ አባት
የምስራች እልል በሉ የ አዳም ልጆችን ሁሉ የምስራች እልል በሉ ክርስቲያኖች ሁሉ🌹
😇ብዙ ልጆች አሉት ለስሙ ምስክር
በዙሪያው ያሉትን አብቅቶል ለክብር
ስለ ፍፁም ምልጃው ለኔ ግን ይለያል
ፃድቁ አባቴ ስለው ደስ ይለኛል😇
ረድኤት በረከቱ አይለየን ::😇🤲😇
👇👇👇👇👇👇👇
@AbuneHabtemariyamtsdik
September 1, 2019
🌹🌹እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም በዓል እና ዘመነ ጽጌ በሰላም በጤና አደረሰን አደረሳችሁ አሜን፡፡🌹🌹🌹
🌼የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን ::
🌷ሰላም ለጻአተ ነፍሰከ እምቤተ ሥጋሃ ንጽሕ:: እሰከነ ትገብእ ድኅረ በትህዛዘ ክርስቶስ መሢሕ:: ሀብተ ማርያም ርግብ ሀብተ ማርያም የዋህ:: አብሥረኒ ብሥራተ ጽድቅ ከመ ብሥራተ አብ ኖኅ::በኂሩተ አምላክ ባዕል ወአኮ በፍትሕ::
🌸ከአሁን በፊት ከሰማይ በታች ያልተሰማ የሚያስደንቅ ነገር በ ደብረ ሊባኖስ ውስጥ ተሰማ በደልን ሁሉ በአማላጅነቱ የሚያስተሰርይ የአባታችን የአቡነ ሀብተማርያምን ድንቅ ስራን የባህር ውሃ መስክራለችና የጻድቁ አባታችን የአቡነ ሀብተማርያም አምላክ እንዲሁም የሁላችን አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ እኛን ልጆችህን ከመከራ ስጋ ከመከራ ነፍስ ሰውረን ከዳቢሎስ ውጊያም ለዘለዓለሙ ጠብቀን ::
🌺ጻዲቁ አቡነ ሀብተማርያም በፈሪሃ እግዚአብሔር በትምህርት አደገ፡፡ ከዕለታት በአንድ ቀን ካህናቱ በቤተክርስቲያን ምህላ ሲያደርሱ "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" እያሉ ሲፀልዩ ሰምቶ በልቡናው ይህች ፀሎት በጣም ጥሩና መልካም ፀሎት ናት አለ በዚህ ፀሎት ከዓለም አሳችነት ከገሃነም እሳት እንድንባት ዘንድ አውቃለሁ የንስሐ መንገድ ናት ብሎ ተናገረ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም በዚህች ፀሎት ተጠምዶ በጾምና በፀሎት በስደት የሚኖር ሆነ::
🌻አምላከ አቡነ ሀብተማርያም ሆይ እኛን ሁላችንን ከተቃጣ መዓት ከታዘዘ መቅሰፍት ከድንገተኛ ሞት ሰውረን ለዘለዓለሙ አሜን::
(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)
🌹ትክበር ነፍስየ በቅድሜከ ዮም
🌹ባርከኒ አባ(5) ሀብተማርያም😇
🌼የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን ::
🌷ሰላም ለጻአተ ነፍሰከ እምቤተ ሥጋሃ ንጽሕ:: እሰከነ ትገብእ ድኅረ በትህዛዘ ክርስቶስ መሢሕ:: ሀብተ ማርያም ርግብ ሀብተ ማርያም የዋህ:: አብሥረኒ ብሥራተ ጽድቅ ከመ ብሥራተ አብ ኖኅ::በኂሩተ አምላክ ባዕል ወአኮ በፍትሕ::
🌸ከአሁን በፊት ከሰማይ በታች ያልተሰማ የሚያስደንቅ ነገር በ ደብረ ሊባኖስ ውስጥ ተሰማ በደልን ሁሉ በአማላጅነቱ የሚያስተሰርይ የአባታችን የአቡነ ሀብተማርያምን ድንቅ ስራን የባህር ውሃ መስክራለችና የጻድቁ አባታችን የአቡነ ሀብተማርያም አምላክ እንዲሁም የሁላችን አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ እኛን ልጆችህን ከመከራ ስጋ ከመከራ ነፍስ ሰውረን ከዳቢሎስ ውጊያም ለዘለዓለሙ ጠብቀን ::
🌺ጻዲቁ አቡነ ሀብተማርያም በፈሪሃ እግዚአብሔር በትምህርት አደገ፡፡ ከዕለታት በአንድ ቀን ካህናቱ በቤተክርስቲያን ምህላ ሲያደርሱ "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" እያሉ ሲፀልዩ ሰምቶ በልቡናው ይህች ፀሎት በጣም ጥሩና መልካም ፀሎት ናት አለ በዚህ ፀሎት ከዓለም አሳችነት ከገሃነም እሳት እንድንባት ዘንድ አውቃለሁ የንስሐ መንገድ ናት ብሎ ተናገረ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም በዚህች ፀሎት ተጠምዶ በጾምና በፀሎት በስደት የሚኖር ሆነ::
🌻አምላከ አቡነ ሀብተማርያም ሆይ እኛን ሁላችንን ከተቃጣ መዓት ከታዘዘ መቅሰፍት ከድንገተኛ ሞት ሰውረን ለዘለዓለሙ አሜን::
(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)
🌹ትክበር ነፍስየ በቅድሜከ ዮም
🌹ባርከኒ አባ(5) ሀብተማርያም😇
October 6, 2019
ጻድቁ አቡነ ሀብተ ማርያም pinned «✝️ክፍል ፩ – የትውልድ ታሪካቸው የቅዱስ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም ትውልድ ሀገር የራውእይ የምትባል ምስራቃዊት ሀገር ውስጥ ሲሆን የኢትዮጵያ ንጉስ እስክንድር በነገሰ በሺ አራት መቶ ሰማንያ ስድስት ዓመተ ምህረት ፍሬ ብሩክ የሚባል አንድ ሰው በዚች ሀገር ውስጥ ነበር፡፡ ይኸውም ከከበሩም ሰዎች ተለይቶ ብዙ ገንዘብ ያለው ባለጸጋ ነበር፡፡ በህጋዊ ጋብቻ ስሟ ዮስቴና የምትባል ሴት አገባ ይህችውም…»
October 15, 2019
🌹እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደረሳችሁ አሜን:፡
🌼የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን ::
🌷ኦ ሚካኤል እግዚእየ ወፍቁርየ ኢትጸመመኒ ወኢትግድፈኒ ውስተጽምዕ ወይኩን ዘአልቦ ረዳኢ::ወሶቤሃ መጽኡ ኅቤሁ 7ቱ ሊቃነ መላእክት እንዘ ሚካኤል ቅድሜሆሙ የሐውር::..."ገድለ አቡነ ሀብተ ማርያም ዘይትነበብ በዕለተ ረቡዕ
🌸ሰላም ለልብከ ለቃለ መጻህፍት ምዕራፍ ::ዘበውስቴታ ይትረከብ መራኁተ ጽድቅ ዘእደ ኬፋ::ሀብተ ማርያም መልአክ ዓቃቤ ትእዛዙ ለአልፋ ይሡቀኒ እምትንታኔ አልብየ ተስፋ::ጸውዖ ስምከ ዘአልቦ ዘለፋ::
🌺ጻዲቁ አቡነ ሀብተማርያም በፈሪሃ እግዚአብሔር በትምህርት አደገ፡፡ ከዕለታት በአንድ ቀን ካህናቱ በቤተክርስቲያን ምህላ ሲያደርሱ "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" እያሉ ሲፀልዩ ሰምቶ በልቡናው ይህች ፀሎት በጣም ጥሩና መልካም ፀሎት ናት አለ በዚህ ፀሎት ከዓለም አሳችነት ከገሃነም እሳት እንድንባት ዘንድ አውቃለሁ የንስሐ መንገድ ናት ብሎ ተናገረ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም በዚህች ፀሎት ተጠምዶ በጾምና በፀሎት በስደት የሚኖር ሆነ::
🌻ኦ አምላከ አቡነ ሀብተ ማርያም ዕቀቦ ወአድኅኖ ወባልሆ እመከራ ሥጋ ወነፍስ ወእምኩሉ ተቃራኒ ወእምኩልነ ክቡር ሀብተ ማርያም ለዓለም ዓለም አሜን ለይኩን ለይኩን::
🕊ቆሜአለሁ ሁልንም አልፌ
😇በምልጃው ከሞት ተርፌ
😇ፀሎቱ ሀይል አደረገልኝ
🕊አቡነ ሀብተ ማርያም እረዳኝ..
🌼የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን ::
🌷ኦ ሚካኤል እግዚእየ ወፍቁርየ ኢትጸመመኒ ወኢትግድፈኒ ውስተጽምዕ ወይኩን ዘአልቦ ረዳኢ::ወሶቤሃ መጽኡ ኅቤሁ 7ቱ ሊቃነ መላእክት እንዘ ሚካኤል ቅድሜሆሙ የሐውር::..."ገድለ አቡነ ሀብተ ማርያም ዘይትነበብ በዕለተ ረቡዕ
🌸ሰላም ለልብከ ለቃለ መጻህፍት ምዕራፍ ::ዘበውስቴታ ይትረከብ መራኁተ ጽድቅ ዘእደ ኬፋ::ሀብተ ማርያም መልአክ ዓቃቤ ትእዛዙ ለአልፋ ይሡቀኒ እምትንታኔ አልብየ ተስፋ::ጸውዖ ስምከ ዘአልቦ ዘለፋ::
🌺ጻዲቁ አቡነ ሀብተማርያም በፈሪሃ እግዚአብሔር በትምህርት አደገ፡፡ ከዕለታት በአንድ ቀን ካህናቱ በቤተክርስቲያን ምህላ ሲያደርሱ "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" እያሉ ሲፀልዩ ሰምቶ በልቡናው ይህች ፀሎት በጣም ጥሩና መልካም ፀሎት ናት አለ በዚህ ፀሎት ከዓለም አሳችነት ከገሃነም እሳት እንድንባት ዘንድ አውቃለሁ የንስሐ መንገድ ናት ብሎ ተናገረ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም በዚህች ፀሎት ተጠምዶ በጾምና በፀሎት በስደት የሚኖር ሆነ::
🌻ኦ አምላከ አቡነ ሀብተ ማርያም ዕቀቦ ወአድኅኖ ወባልሆ እመከራ ሥጋ ወነፍስ ወእምኩሉ ተቃራኒ ወእምኩልነ ክቡር ሀብተ ማርያም ለዓለም ዓለም አሜን ለይኩን ለይኩን::
🕊ቆሜአለሁ ሁልንም አልፌ
😇በምልጃው ከሞት ተርፌ
😇ፀሎቱ ሀይል አደረገልኝ
🕊አቡነ ሀብተ ማርያም እረዳኝ..
November 6, 2019
ጻድቁ አቡነ ሀብተ ማርያም pinned «🌹እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደረሳችሁ አሜን:፡ 🌼የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን :: 🌷ኦ ሚካኤል እግዚእየ ወፍቁርየ ኢትጸመመኒ ወኢትግድፈኒ ውስተጽምዕ ወይኩን…»
November 7, 2019
November 14, 2019
➬እንካን አደረሳችሁ ህዳር 26 የፃዲቁ በዓለ እረፍት
#ኢትዮጵያዊው_ፃዲቅ_አቡነ_ሀብተማርያም
➬እኒህ ጻድቅ ደግሞ የሃገራችን ኮከበ ገዳም ናቸው:: "ጽድቅና ትሩፋት እንደ ሃብተ ማርያም" እንዲሉ አበው:: ባሕር ከሆነ ጣዕመ ሕይወታቸው ጥቂቱን ለበረከት እንካፈል::
ጻድቁ መካነ ሙላዳቸው ሽዋ (የራውዕይ) ውስጥ ሲሆን አባታቸው ፍሬ ቡሩክ: እናታቸውት ደግሞ ቅድስት ዮስቴና ትባላለች:: በተለይ ቅድስት ዮስቴና እጅግ ደመ ግቡ: ምጽዋትን ወዳጅ: ቡርክት ሴት ነበረች:: እንዲያውም ከጻድቁ መወለድ በፊት መንና ጭው ካለ በርሃ ገብታ ነበር::
+ግን የበቃ ግኁስ አግኝቷት "ከማሕጸንሽ ደግ የሥላሴ ባርያ አለና ተመለሽ" ብሏት እንደ ገና ተመልሳለች:: ጻድቁን ወልዳ አሳድጋም እንደ ገና መንና በተጋድሎ ኑራ 7 አክሊላትን ተቀብላ ዐርፋለች::
+ወደ ጻድቁ ዜና ሕይወት ስንመለስ አቡነ ሃብተ ማርያም ገና ሕጻን እያሉ ከእናታቸው ጋር ቆመው ሲያስቀድሱ "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" ሲባል ይሰማሉ:: ይሕችን ጸሎት በሕጻን አንደበታቸው ይዘው ሌሊት ሌሊት እየተነሱ "ማረን እባክህን?" እያሉ ይሰግዱ ነበር::
+የ5 ዓመት ሕጻን እንዲህ ሲያደርግ ማየቱ በእውነት ይደንቃል:: ትንሽ ከፍ ብለው በእረኝነት ሳሉም ፍጹም ተሐራሚና ጸዋሚ ነበሩ:: ጸጋው ስለ በዛላቸውም ልጅ ሆነው ብዙ ተአምራትን ሰርተዋል:: የፈጣሪውን ስም ያቃለውን አንድ እረኛም በዓየር ላይ ሰቅለው አውለውታል::
+ከዚያ ግን ለአካለ መጠን ሲደርሱ ወደ ት/ቤት ገብተው: መጻሕፍትንም አጥንተው መንነዋል:: በአባ መልከ ጼዴቅ እጅ ከመነኮሱ በሁዋላ የሠሩትን ትሩፋትና የነበራቸውን ተጋድሎ ግን የኔ ብጤ ደካማ ሰው ሊዘረዝረው አይችልም::
*ባሕር ውስጥ ሰጥመው 500 ጊዜ ይሰግዳሉ::
*በየቀኑ 4ቱን ወንጌልና 150 መዝሙረ ዳዊትን ይጸልያሉ:: (መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ታላቅ ጸሎት ነው)
*በ40 ቀናት: ቀጥሎም በ80 ቀን አንዴ ብቻ ይመገባሉ::
*ምግባቸው ደግሞ ሣርና ቅጠል ብቻ ነው::
*በየዕለቱ ያለ ማስታጐል ማዕጠንት ያሳርጋሉ:: (ካህን ናቸውና)
*ዘወትር በንጽሕና ቅዱስ ሥጋውን ይበላሉ: ክቡር ደሙን ይጠጣሉ::
*በፍጹም በልባቸው ውስጥ ቂምን: መከፋትን አላሳደሩም::
+በእነዚህና በሌሎች ትሩፋቶቻቸው ደስ የተሰኘ ጌታም ለጻድቁ የእሳትና የብርሃን ሠረገላን ሰጥቷቸው በዚያ እየበረሩ ኢየሩሳሌም ይሔዱ ነበር:: ከብዙ የተጋድሎ ዘመናት በሁዋላም የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ አዕላፍ መላእክትን አስከተትሎ መጥቶ አላቸው::
+"*ስለ እኔ ረሃብና ጥምን ስለ ታገስክ: *ስለ ምናኔሕ: *ስለ ተባረከ ምንኩስናህ: *ስለ ንጹሕ ድንግልናህ: *ቂምና በቀልን ስላለመያዝህ: *ስለ ንጹሕ ክህነትህና ማዕጠንትህ: *ቅዱስ ወንጌልን በፍቅር ስለ ማንበብህ 7 አክሊላትን እሰጥሃለሁ::"
+"በሰማይም ከመጥምቁ ዮሐንስ ጐን: 500 የእንቁ ምሰሶዎች ያሉበትን አዳራሽ ሰጥቼሃለሁ:: በስምህ የሚለምኑ: በቃል ኪዳንህ የሚማጸኑትንም ሁሉ እንድምርልህ 'አማንየ! በርእስየ!' ብዬሃለሁ" አላቸው::
+ቅዱሳን መላእክትም "ሃብተ ማርያም ወንድማችን" ሲሉ አቀፏቸው:: ጌታ ግን በዚያች ሰዓት አንድም ሦስትም ሆኖ ታያቸውና አቅፎ 3 ጊዜ ፨ንን የተመለከቱ የናግራን ክርስቲያኖች ግን ስለ መፍራት ፈንታ በፈቃዳቸው እየተሯሯጡ ወደ እሳትና ሰይፍ ተሽቀዳደሙ::
+ከተማዋም እየነደደችና ደም እየፈሰሰባት ለ40 ቀናት ቆየች:: ይሕንን የሰማው ቅዱሱ አፄ ካሌብም ደርሶ የተረፉትን ሲታደግ ፊንሐስን ከነ ወታደሮቹ አጥፍቶታል::
=>አምላከ አበው ወሰማዕት ጣዕመ ፍቅራቸውን: ክብራቸውን: ጸጋ በረከታቸውንም ይክፈለን::
አሜን አሜን አሜን
#ኢትዮጵያዊው_ፃዲቅ_አቡነ_ሀብተማርያም
➬እኒህ ጻድቅ ደግሞ የሃገራችን ኮከበ ገዳም ናቸው:: "ጽድቅና ትሩፋት እንደ ሃብተ ማርያም" እንዲሉ አበው:: ባሕር ከሆነ ጣዕመ ሕይወታቸው ጥቂቱን ለበረከት እንካፈል::
ጻድቁ መካነ ሙላዳቸው ሽዋ (የራውዕይ) ውስጥ ሲሆን አባታቸው ፍሬ ቡሩክ: እናታቸውት ደግሞ ቅድስት ዮስቴና ትባላለች:: በተለይ ቅድስት ዮስቴና እጅግ ደመ ግቡ: ምጽዋትን ወዳጅ: ቡርክት ሴት ነበረች:: እንዲያውም ከጻድቁ መወለድ በፊት መንና ጭው ካለ በርሃ ገብታ ነበር::
+ግን የበቃ ግኁስ አግኝቷት "ከማሕጸንሽ ደግ የሥላሴ ባርያ አለና ተመለሽ" ብሏት እንደ ገና ተመልሳለች:: ጻድቁን ወልዳ አሳድጋም እንደ ገና መንና በተጋድሎ ኑራ 7 አክሊላትን ተቀብላ ዐርፋለች::
+ወደ ጻድቁ ዜና ሕይወት ስንመለስ አቡነ ሃብተ ማርያም ገና ሕጻን እያሉ ከእናታቸው ጋር ቆመው ሲያስቀድሱ "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" ሲባል ይሰማሉ:: ይሕችን ጸሎት በሕጻን አንደበታቸው ይዘው ሌሊት ሌሊት እየተነሱ "ማረን እባክህን?" እያሉ ይሰግዱ ነበር::
+የ5 ዓመት ሕጻን እንዲህ ሲያደርግ ማየቱ በእውነት ይደንቃል:: ትንሽ ከፍ ብለው በእረኝነት ሳሉም ፍጹም ተሐራሚና ጸዋሚ ነበሩ:: ጸጋው ስለ በዛላቸውም ልጅ ሆነው ብዙ ተአምራትን ሰርተዋል:: የፈጣሪውን ስም ያቃለውን አንድ እረኛም በዓየር ላይ ሰቅለው አውለውታል::
+ከዚያ ግን ለአካለ መጠን ሲደርሱ ወደ ት/ቤት ገብተው: መጻሕፍትንም አጥንተው መንነዋል:: በአባ መልከ ጼዴቅ እጅ ከመነኮሱ በሁዋላ የሠሩትን ትሩፋትና የነበራቸውን ተጋድሎ ግን የኔ ብጤ ደካማ ሰው ሊዘረዝረው አይችልም::
*ባሕር ውስጥ ሰጥመው 500 ጊዜ ይሰግዳሉ::
*በየቀኑ 4ቱን ወንጌልና 150 መዝሙረ ዳዊትን ይጸልያሉ:: (መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ታላቅ ጸሎት ነው)
*በ40 ቀናት: ቀጥሎም በ80 ቀን አንዴ ብቻ ይመገባሉ::
*ምግባቸው ደግሞ ሣርና ቅጠል ብቻ ነው::
*በየዕለቱ ያለ ማስታጐል ማዕጠንት ያሳርጋሉ:: (ካህን ናቸውና)
*ዘወትር በንጽሕና ቅዱስ ሥጋውን ይበላሉ: ክቡር ደሙን ይጠጣሉ::
*በፍጹም በልባቸው ውስጥ ቂምን: መከፋትን አላሳደሩም::
+በእነዚህና በሌሎች ትሩፋቶቻቸው ደስ የተሰኘ ጌታም ለጻድቁ የእሳትና የብርሃን ሠረገላን ሰጥቷቸው በዚያ እየበረሩ ኢየሩሳሌም ይሔዱ ነበር:: ከብዙ የተጋድሎ ዘመናት በሁዋላም የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ አዕላፍ መላእክትን አስከተትሎ መጥቶ አላቸው::
+"*ስለ እኔ ረሃብና ጥምን ስለ ታገስክ: *ስለ ምናኔሕ: *ስለ ተባረከ ምንኩስናህ: *ስለ ንጹሕ ድንግልናህ: *ቂምና በቀልን ስላለመያዝህ: *ስለ ንጹሕ ክህነትህና ማዕጠንትህ: *ቅዱስ ወንጌልን በፍቅር ስለ ማንበብህ 7 አክሊላትን እሰጥሃለሁ::"
+"በሰማይም ከመጥምቁ ዮሐንስ ጐን: 500 የእንቁ ምሰሶዎች ያሉበትን አዳራሽ ሰጥቼሃለሁ:: በስምህ የሚለምኑ: በቃል ኪዳንህ የሚማጸኑትንም ሁሉ እንድምርልህ 'አማንየ! በርእስየ!' ብዬሃለሁ" አላቸው::
+ቅዱሳን መላእክትም "ሃብተ ማርያም ወንድማችን" ሲሉ አቀፏቸው:: ጌታ ግን በዚያች ሰዓት አንድም ሦስትም ሆኖ ታያቸውና አቅፎ 3 ጊዜ ፨ንን የተመለከቱ የናግራን ክርስቲያኖች ግን ስለ መፍራት ፈንታ በፈቃዳቸው እየተሯሯጡ ወደ እሳትና ሰይፍ ተሽቀዳደሙ::
+ከተማዋም እየነደደችና ደም እየፈሰሰባት ለ40 ቀናት ቆየች:: ይሕንን የሰማው ቅዱሱ አፄ ካሌብም ደርሶ የተረፉትን ሲታደግ ፊንሐስን ከነ ወታደሮቹ አጥፍቶታል::
=>አምላከ አበው ወሰማዕት ጣዕመ ፍቅራቸውን: ክብራቸውን: ጸጋ በረከታቸውንም ይክፈለን::
አሜን አሜን አሜን
December 5, 2019
ጻድቁ አቡነ ሀብተ ማርያም pinned «➬እንካን አደረሳችሁ ህዳር 26 የፃዲቁ በዓለ እረፍት #ኢትዮጵያዊው_ፃዲቅ_አቡነ_ሀብተማርያም ➬እኒህ ጻድቅ ደግሞ የሃገራችን ኮከበ ገዳም ናቸው:: "ጽድቅና ትሩፋት እንደ ሃብተ ማርያም" እንዲሉ አበው:: ባሕር ከሆነ ጣዕመ ሕይወታቸው ጥቂቱን ለበረከት እንካፈል:: ጻድቁ መካነ ሙላዳቸው ሽዋ (የራውዕይ) ውስጥ ሲሆን አባታቸው ፍሬ ቡሩክ: እናታቸውት ደግሞ ቅድስት ዮስቴና ትባላለች:: በተለይ ቅድስት ዮስቴና…»
ፃድቁ አባታቻን አቡነ ሀብተ ማርያም:-
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ኅዳር ሃያ ስድስት በዚህች ቀን የተመሰገነ የከበረ ንጹሕም የሆነ
የኢትዮጵያው አባታቻን የሀብተ ማርያም የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው::
የዚህ ቅዱስ አባት ትውልድ አገሩ የራውዕይ በምትባል በስተ ምሥራቅ ባለች ሀገር ውስጥ ነው:: በዚያም ፍሬ ቡሩክ የሚባል አንድ ሰው ነበረ ከዚች አገር ታላላቅ ሰዎች አንዱ ነው::
እጅግም ሀብታም ነበር ብዙ ንብረትም አለው በሕጋዊ ጋብቻም ስሟ ዮስቴና የምትባል ብላቴና ድንግልን አገባ ይቺም የተመረጠች በበጎ ሥራ የተሸለመችና ያጌጠች ናት::
ነገር ግን አስቀድመን በዚህ ዓለም ከሕግ ባሏ ጋር በንጹሕ ጋብቻ እግዚአብሔርን በመፍራት ምጽዋትን በመስጠት የዋህነትን ትሕትናን ፍቅርን ትዕግስትን ገንዘብ አድርጋ በጾም በጸሎት ተወስና ኖረች::
በእንደዚህም ሳለች ጌታችን በወንጌል ሰው ዓለሙን ቢያተርፍ ነፍሱን ካጠፋ ምን ይጠቅመዋል እንዳለ ላንቺ በዚህ ዓለም መኖር ምን ይረባሽ የሚል ሐሳብ መጣባት::
ከዚህም በኋላ ወጣች ፈጥናም በሀገርዋ ትይዩ ወደ ሆነ ምድረ በዳ ደርሳ ወደ መካከሉ ገባች::
በዚያም በረሀ አራዊት እንጂ ሰው አይኖርበትም በዚያም ደጃፍዋ የተከፈተ ታናሽ ዋሻ አግኝታ ምንም ምን ሳትነጋገር ወደ ውስጧ ገብታ ቆመች የዳዊትንም መዝሙር የሚጸልይ ሰው አይታ ደነገጠች እርሱም ባያት ጊዜ ፍርዓትና መንቀጥቀጥ በላዩ ወረደበት በመስቀል ምልክትም በላይዋ አማትቦ የእግዚአብሔርን ስም ጠራ እንዳልሸሸችም አይቶ ሰው መሆንዋን አወቀ በአወቀም ጊዜ እንዲህ ብሎ ገሠጻት ወደዚህ ምን አመጣሽ ለእኔ እንቅፋት ልትሆኚ ነውን አሁንም ከዚህ ፈጥነሽ ሒጂ አላት::
እርሷም አባቴ ሆይ አንተ እንዳሰብከው አይደለሁም እኔ ለሕያው እግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ነኝ እንጂ በእርሱ ፍቅርና በእናቱ በእመቤቴ በቅድስት ድንግል ማርያም ፍቅር ያለኝን ሁሉ ትቼ ንቄ ከዓለም ወጥቼ ወደዚህ መጣሁ በዚህ ቦታም ከአራዊት በቀር ሰው እንዳለ አላወቅሁም አሁንም አባቴ ይቅርታ አድርግልኝ ወደ ሌላ ቦታ ልሔድ አለችው።
ይህም አባት መንፈስ ቅዱስ በገለጠለት መሠረት እንዲህ አላት ዜናው ወደ ዓለም ሁሉ የሚወጣ በሕይወተ ሥጋም እያለ የብዙዎች ሰዎች ነፍስን ከሲኦል የሚያወጣ እንደ መላእክትም ክንፎች ተሰጥተውት ወደ አርያም ወጥቶ የሥላሴን የአንድነትና የሦስትነት ምሥጢር የሚያይ ልጅን ትወልጂ ዘንድ አለሽና ወደ ቤትሽ ተመለሽ አላት::
ቅድስ ዮስቴናም ከዚያ ሽማግሌ ባሕታዊ ይህን በሰማች ጊዜ አድንቃ የፈጣሪዬ ፈቃዱ ከሆነ ብላ ወደቤቷ ተመለሰች::
ከጥቂት ቀኖችም በኋላ ፀንሳ ይህን ደምግባቱ መልኩ የሚያምር ልጅን ወለደች በእናትና በአባቱ ቤትም ታላቅ ደስታ ሁኖ ለድኆችና ለጦም አዳሪዎች ለዘመዶቻቸውና ለጎረቤቶቻቸው ታላቅ ምሳ አደረጉ እነርሱም በጠገቡ ጊዜ እነርሱንም ሕፃኑንም መረቋቸው::
ሕፃኑም አርባ ቀን በሆነው ጊዜ እንደ ሕጉና እንደ ሕጉና እንደ ሥርዓቱ ወደ ቤተ ክርስቲያን ወሰዱት ካህኑም ተቀብሎ በአጠመቀው ጊዜ ስሙን ሀብተ ማርያም ብሎ ሰየመው ለክርስትና አባቱ ሰጠው ሕፃኑም ጥቂት በአደገ ጊዜ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ ሲሉ ሰምቶ ሕፃን ሀብተ ማርያም በልቡ ይቺ ጸሎት መልካም ናት እኔም መርጫታለሁ በዚህ ዓለም ስሕተትን አስቦ ከመሥራት በሚመጣው ዓለም ከገሀነም እንደምድንባት አውቃለሁና አለ::
ይህንንም ብሎ የሚሠራውን ማንም ሳያውቅበት ይህን ጸሎት ከማዘውተር ጋር ሌሊቱን ሁሉ በመስገድ ይጸልይ ነበር::
ከረጅም ዘመናት በኋላ ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ሒዶ ከዚያም የምንኵስናን ሥርዓትና ሕግ በአበምኔቱ በተመረጠ አባ መልከጼዴቅ እጅ ተቀበለ ከዚያም ቅዱሳን መነኰሳት ወደሚኖሩበት ሔዶ ታላቅ ተጋድሎ ጀመረ::
እርሱም በባሕር መካከል በመቆም የዳዊትን መዝሙር ሁሉንም ያነባል በባሕር ውስጥም ሰጥሞ ግምባሩ አሸዋ እስቲነካው አምስት መቶ ጊዜ ይሰግዳል ከሰንበት ቀኖችም በቀር እህል አይቀምስም ነበር:: ከዚህም በኋላ እህልን ትቶ እንደ ወልያዎች የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ::
አርባ አርባ ሰማንያ ሰማንያ ቀን የሚጾምበት ቀን ጊዜ አለ በባሕር ውስጥ በሌሊት ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ያነባል ሌሎች መጻሕፍትንም በእንዲህ ያለ ሥራ ብዙ ዘመን ኖረ::
ብዙ ተጋድሎንና ድካምንም በአስረዘመ ጊዜ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ወደርሱ ተገልጦ መጣ ከእርሱ ጋርም የመላእክት አለቆች የከበሩ ሚካኤልና ገብርኤል የመላእክት ማኅበርም ሁሉ በዙራሪያው ሁነው እያመሰገኑት ነበር::
ወዳጄ ሀብተ ማርያም ሰላም ላንተ ይሁን አለው:: በዚያም ጊዜ ከግርማው የተነሣ ወድቆ እንደ በድን ሆነ ጌታችንም እጆቹ አንሥቶ እፍ አለበትና ጽና ኃይልህን ላድሳት እንጂ ላጠፋህ አልመጣሁምና ተጋድሎህና ድካምህ ሁሉ በኢየሩሳሌም ሰማያዊት እንደ ተጻፈ በእውነት እነግርሃለሁ::
እንሆ እኔ በጎ ዋጋህን በዚህም ዓለም በሚመጣው ዓለም እከፍልሃለሁ የማቴዎስንና የማርቆስን ወንጌል በምታነብ ጊዜ በተራራዎችና በዋሻዎች በፍርኩታ ተሠወረው ወደሚኖሩ እንዳንተ ካሉ ቅዱሳን ጋር ለመገናኘት በላዩ ተቀምጠህ ወደ ምሥራቅ ወደ ምዕራብ ወደ ሰሜንና ደቡብ የምትበርበት የብርሃን ሠረገላ ሰጠሁህ ሉቃስና ዮሐንስ የጻፉትን ወንጌል ባነበብክ ጊዜ ሥጋዬንና ደሜን በዚያ ትቀበል ዘንድ በላዩ ተቀምጠህ ወደ ኢየሩሳሌም የምትሔድበት የእሳት ሠረገላ ሰጠሁህ አለው::
ከብዙ ዘመናት ከብዙ ተጋድሎ በኃላ የሚሞትበት ጊዜ ሲደርስ ለሞቱ ምክንያት የሚሆን ቸነፈር ያዘው::
ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ እርሱ መጥቶ ወዳጄ ሀብተ ማርያም ሰላም ላንተ ይሁን:: ዛሬ ግን የመጣሁት ከድካምህ ወደ ሕረፍት ልወስድህ ነው:: እንሆ ሰባት አክሊላትን አዘጋጅቼልሃለው::
አንዱ ስለድንግልናህ:: ሁለተኛው ዓለምንና በውስጧ ያለውን ትተህ በመውጣትህ:: ሦስተኛ ፍጹም ስለሆነው ምንኵስናህ:: አራተኛው አራቱን ወንጌሎች አዘውትረህ በማንበብህ:: አምስተኛው ስለኔ ፍቅር መራብና መጠማትን ስለታገሥክ:: ስድስተኛው በልብህ ቂምና በቀል ስላለማሳደርህ:: ሰባተኛው ስለ ንጹሕ ክህነትህና ስለምታሳርገው ያማረ የተወደደ መስዋትህ ሰጠሁህ:: እሊህ ሰባቱ አክሊላትም ለእያንዳንዳቸው ዐሥራ አምስት ዐሥራ አምስት ኅብር አላቸው::
መታሰቢያህን ካደረጉና በጸሎትህ ከተማፀኑ ጋር የምትገባበትን ቤት በውስጧ አምስት መቶ የወርቅ አምዶች የተተከሉባትን ሰጠሁህ ደግሞ የእሳት መስቀልን የወርቅ ጫማን የብርሃን ልብስን ሥውር የሆነ መና እሰጥሃለሁ አለው::
መድኃኒታችን ይህን ቃል ሲሰጠው በየነገዳቸውና በየሥርዓታቸው ዘጠና ዘጠኝ የመላእክት ሠራዊት መጥተው ወዳጃችን ሰላም ላንተ ይሁን ዛሬስ ከፀሐይ ሰባት እጅ ወደምታበራ ሀገራችን በዝማሬና በማኅሌት አክብረን ልንወስድህ መጣን አሉት::
አባታችን አባ ሀብተ ማርያምም በሰማያት ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በምድርም ሰላም ሆነ የሰው ነጻነቱን ሊሰጠው አለ::
ይህንንም በተናገረ ጊዜ ጌታችን በሦስትነቱ ተገልጦ ታየውና የመጥምቁ ዮሐንስን ሀገር ተጠጋግታ ያለች ከፀሐይ ሰባት እጅ የምታበራ ሀገርን እሰጥህ ዘንድ በራሴ ማልኩልህ አለው::
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ኅዳር ሃያ ስድስት በዚህች ቀን የተመሰገነ የከበረ ንጹሕም የሆነ
የኢትዮጵያው አባታቻን የሀብተ ማርያም የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው::
የዚህ ቅዱስ አባት ትውልድ አገሩ የራውዕይ በምትባል በስተ ምሥራቅ ባለች ሀገር ውስጥ ነው:: በዚያም ፍሬ ቡሩክ የሚባል አንድ ሰው ነበረ ከዚች አገር ታላላቅ ሰዎች አንዱ ነው::
እጅግም ሀብታም ነበር ብዙ ንብረትም አለው በሕጋዊ ጋብቻም ስሟ ዮስቴና የምትባል ብላቴና ድንግልን አገባ ይቺም የተመረጠች በበጎ ሥራ የተሸለመችና ያጌጠች ናት::
ነገር ግን አስቀድመን በዚህ ዓለም ከሕግ ባሏ ጋር በንጹሕ ጋብቻ እግዚአብሔርን በመፍራት ምጽዋትን በመስጠት የዋህነትን ትሕትናን ፍቅርን ትዕግስትን ገንዘብ አድርጋ በጾም በጸሎት ተወስና ኖረች::
በእንደዚህም ሳለች ጌታችን በወንጌል ሰው ዓለሙን ቢያተርፍ ነፍሱን ካጠፋ ምን ይጠቅመዋል እንዳለ ላንቺ በዚህ ዓለም መኖር ምን ይረባሽ የሚል ሐሳብ መጣባት::
ከዚህም በኋላ ወጣች ፈጥናም በሀገርዋ ትይዩ ወደ ሆነ ምድረ በዳ ደርሳ ወደ መካከሉ ገባች::
በዚያም በረሀ አራዊት እንጂ ሰው አይኖርበትም በዚያም ደጃፍዋ የተከፈተ ታናሽ ዋሻ አግኝታ ምንም ምን ሳትነጋገር ወደ ውስጧ ገብታ ቆመች የዳዊትንም መዝሙር የሚጸልይ ሰው አይታ ደነገጠች እርሱም ባያት ጊዜ ፍርዓትና መንቀጥቀጥ በላዩ ወረደበት በመስቀል ምልክትም በላይዋ አማትቦ የእግዚአብሔርን ስም ጠራ እንዳልሸሸችም አይቶ ሰው መሆንዋን አወቀ በአወቀም ጊዜ እንዲህ ብሎ ገሠጻት ወደዚህ ምን አመጣሽ ለእኔ እንቅፋት ልትሆኚ ነውን አሁንም ከዚህ ፈጥነሽ ሒጂ አላት::
እርሷም አባቴ ሆይ አንተ እንዳሰብከው አይደለሁም እኔ ለሕያው እግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ነኝ እንጂ በእርሱ ፍቅርና በእናቱ በእመቤቴ በቅድስት ድንግል ማርያም ፍቅር ያለኝን ሁሉ ትቼ ንቄ ከዓለም ወጥቼ ወደዚህ መጣሁ በዚህ ቦታም ከአራዊት በቀር ሰው እንዳለ አላወቅሁም አሁንም አባቴ ይቅርታ አድርግልኝ ወደ ሌላ ቦታ ልሔድ አለችው።
ይህም አባት መንፈስ ቅዱስ በገለጠለት መሠረት እንዲህ አላት ዜናው ወደ ዓለም ሁሉ የሚወጣ በሕይወተ ሥጋም እያለ የብዙዎች ሰዎች ነፍስን ከሲኦል የሚያወጣ እንደ መላእክትም ክንፎች ተሰጥተውት ወደ አርያም ወጥቶ የሥላሴን የአንድነትና የሦስትነት ምሥጢር የሚያይ ልጅን ትወልጂ ዘንድ አለሽና ወደ ቤትሽ ተመለሽ አላት::
ቅድስ ዮስቴናም ከዚያ ሽማግሌ ባሕታዊ ይህን በሰማች ጊዜ አድንቃ የፈጣሪዬ ፈቃዱ ከሆነ ብላ ወደቤቷ ተመለሰች::
ከጥቂት ቀኖችም በኋላ ፀንሳ ይህን ደምግባቱ መልኩ የሚያምር ልጅን ወለደች በእናትና በአባቱ ቤትም ታላቅ ደስታ ሁኖ ለድኆችና ለጦም አዳሪዎች ለዘመዶቻቸውና ለጎረቤቶቻቸው ታላቅ ምሳ አደረጉ እነርሱም በጠገቡ ጊዜ እነርሱንም ሕፃኑንም መረቋቸው::
ሕፃኑም አርባ ቀን በሆነው ጊዜ እንደ ሕጉና እንደ ሕጉና እንደ ሥርዓቱ ወደ ቤተ ክርስቲያን ወሰዱት ካህኑም ተቀብሎ በአጠመቀው ጊዜ ስሙን ሀብተ ማርያም ብሎ ሰየመው ለክርስትና አባቱ ሰጠው ሕፃኑም ጥቂት በአደገ ጊዜ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ ሲሉ ሰምቶ ሕፃን ሀብተ ማርያም በልቡ ይቺ ጸሎት መልካም ናት እኔም መርጫታለሁ በዚህ ዓለም ስሕተትን አስቦ ከመሥራት በሚመጣው ዓለም ከገሀነም እንደምድንባት አውቃለሁና አለ::
ይህንንም ብሎ የሚሠራውን ማንም ሳያውቅበት ይህን ጸሎት ከማዘውተር ጋር ሌሊቱን ሁሉ በመስገድ ይጸልይ ነበር::
ከረጅም ዘመናት በኋላ ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ሒዶ ከዚያም የምንኵስናን ሥርዓትና ሕግ በአበምኔቱ በተመረጠ አባ መልከጼዴቅ እጅ ተቀበለ ከዚያም ቅዱሳን መነኰሳት ወደሚኖሩበት ሔዶ ታላቅ ተጋድሎ ጀመረ::
እርሱም በባሕር መካከል በመቆም የዳዊትን መዝሙር ሁሉንም ያነባል በባሕር ውስጥም ሰጥሞ ግምባሩ አሸዋ እስቲነካው አምስት መቶ ጊዜ ይሰግዳል ከሰንበት ቀኖችም በቀር እህል አይቀምስም ነበር:: ከዚህም በኋላ እህልን ትቶ እንደ ወልያዎች የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ::
አርባ አርባ ሰማንያ ሰማንያ ቀን የሚጾምበት ቀን ጊዜ አለ በባሕር ውስጥ በሌሊት ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ያነባል ሌሎች መጻሕፍትንም በእንዲህ ያለ ሥራ ብዙ ዘመን ኖረ::
ብዙ ተጋድሎንና ድካምንም በአስረዘመ ጊዜ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ወደርሱ ተገልጦ መጣ ከእርሱ ጋርም የመላእክት አለቆች የከበሩ ሚካኤልና ገብርኤል የመላእክት ማኅበርም ሁሉ በዙራሪያው ሁነው እያመሰገኑት ነበር::
ወዳጄ ሀብተ ማርያም ሰላም ላንተ ይሁን አለው:: በዚያም ጊዜ ከግርማው የተነሣ ወድቆ እንደ በድን ሆነ ጌታችንም እጆቹ አንሥቶ እፍ አለበትና ጽና ኃይልህን ላድሳት እንጂ ላጠፋህ አልመጣሁምና ተጋድሎህና ድካምህ ሁሉ በኢየሩሳሌም ሰማያዊት እንደ ተጻፈ በእውነት እነግርሃለሁ::
እንሆ እኔ በጎ ዋጋህን በዚህም ዓለም በሚመጣው ዓለም እከፍልሃለሁ የማቴዎስንና የማርቆስን ወንጌል በምታነብ ጊዜ በተራራዎችና በዋሻዎች በፍርኩታ ተሠወረው ወደሚኖሩ እንዳንተ ካሉ ቅዱሳን ጋር ለመገናኘት በላዩ ተቀምጠህ ወደ ምሥራቅ ወደ ምዕራብ ወደ ሰሜንና ደቡብ የምትበርበት የብርሃን ሠረገላ ሰጠሁህ ሉቃስና ዮሐንስ የጻፉትን ወንጌል ባነበብክ ጊዜ ሥጋዬንና ደሜን በዚያ ትቀበል ዘንድ በላዩ ተቀምጠህ ወደ ኢየሩሳሌም የምትሔድበት የእሳት ሠረገላ ሰጠሁህ አለው::
ከብዙ ዘመናት ከብዙ ተጋድሎ በኃላ የሚሞትበት ጊዜ ሲደርስ ለሞቱ ምክንያት የሚሆን ቸነፈር ያዘው::
ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ እርሱ መጥቶ ወዳጄ ሀብተ ማርያም ሰላም ላንተ ይሁን:: ዛሬ ግን የመጣሁት ከድካምህ ወደ ሕረፍት ልወስድህ ነው:: እንሆ ሰባት አክሊላትን አዘጋጅቼልሃለው::
አንዱ ስለድንግልናህ:: ሁለተኛው ዓለምንና በውስጧ ያለውን ትተህ በመውጣትህ:: ሦስተኛ ፍጹም ስለሆነው ምንኵስናህ:: አራተኛው አራቱን ወንጌሎች አዘውትረህ በማንበብህ:: አምስተኛው ስለኔ ፍቅር መራብና መጠማትን ስለታገሥክ:: ስድስተኛው በልብህ ቂምና በቀል ስላለማሳደርህ:: ሰባተኛው ስለ ንጹሕ ክህነትህና ስለምታሳርገው ያማረ የተወደደ መስዋትህ ሰጠሁህ:: እሊህ ሰባቱ አክሊላትም ለእያንዳንዳቸው ዐሥራ አምስት ዐሥራ አምስት ኅብር አላቸው::
መታሰቢያህን ካደረጉና በጸሎትህ ከተማፀኑ ጋር የምትገባበትን ቤት በውስጧ አምስት መቶ የወርቅ አምዶች የተተከሉባትን ሰጠሁህ ደግሞ የእሳት መስቀልን የወርቅ ጫማን የብርሃን ልብስን ሥውር የሆነ መና እሰጥሃለሁ አለው::
መድኃኒታችን ይህን ቃል ሲሰጠው በየነገዳቸውና በየሥርዓታቸው ዘጠና ዘጠኝ የመላእክት ሠራዊት መጥተው ወዳጃችን ሰላም ላንተ ይሁን ዛሬስ ከፀሐይ ሰባት እጅ ወደምታበራ ሀገራችን በዝማሬና በማኅሌት አክብረን ልንወስድህ መጣን አሉት::
አባታችን አባ ሀብተ ማርያምም በሰማያት ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በምድርም ሰላም ሆነ የሰው ነጻነቱን ሊሰጠው አለ::
ይህንንም በተናገረ ጊዜ ጌታችን በሦስትነቱ ተገልጦ ታየውና የመጥምቁ ዮሐንስን ሀገር ተጠጋግታ ያለች ከፀሐይ ሰባት እጅ የምታበራ ሀገርን እሰጥህ ዘንድ በራሴ ማልኩልህ አለው::
December 6, 2019
መታሰቢያህን የሚያደርገውን በስምህ ለቤተ ክርስቲያን መባ የሚሰጠውን ስምህንም የሚጠራውን ወደዚህች ሀገር አገባዋለሁ::
አራቱ ወንጌሎችንም እያነበብክ ስለኖርክ የየአንዲቱን ፍሬዋን አንድ አንድ ሺ አደረግሁልህ ይኽውም ካንተ በኋላ ለሚመጡ ልጆችህ መጽሐፈ ገድልህን ለሚያነቡና ለሚሰሙ የገድልህን መጽሐፍ በተነበበት ውኃ ለሚረጩ ለሚነከሩበት ይህን ቃል ኪዳን ሰጥቼሃለሁ::
ከዚህ በኋላ መድኃኒታችን ነፍሱን ተቀብሎ አቅፎ ከእርሱ ጋር አሳረጋት:: በመላእክት ጉባኤም ብዙ ምስጋና ተደረገ:: ሥጋው በደብረ ሊባኖስ ገዳም በክብር ተቀመጠ::
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በፃድቁ ሀብተ ማርያም ጸሎት ይማረን ቃል ኪዳኑም ይሁን ይፈጸምልን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን::
Source : -@ethiopianorthodoxs⛪️⛪️
አራቱ ወንጌሎችንም እያነበብክ ስለኖርክ የየአንዲቱን ፍሬዋን አንድ አንድ ሺ አደረግሁልህ ይኽውም ካንተ በኋላ ለሚመጡ ልጆችህ መጽሐፈ ገድልህን ለሚያነቡና ለሚሰሙ የገድልህን መጽሐፍ በተነበበት ውኃ ለሚረጩ ለሚነከሩበት ይህን ቃል ኪዳን ሰጥቼሃለሁ::
ከዚህ በኋላ መድኃኒታችን ነፍሱን ተቀብሎ አቅፎ ከእርሱ ጋር አሳረጋት:: በመላእክት ጉባኤም ብዙ ምስጋና ተደረገ:: ሥጋው በደብረ ሊባኖስ ገዳም በክብር ተቀመጠ::
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በፃድቁ ሀብተ ማርያም ጸሎት ይማረን ቃል ኪዳኑም ይሁን ይፈጸምልን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን::
Source : -@ethiopianorthodoxs⛪️⛪️
🔔🕡🕡እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም በዓል አደረሰን አደረሳችሁ አሜን፡፡
🌼የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን ::
🌷ሰላም ለጻአተ ነፍሰከ እምቤተ ሥጋሃ ንጽሕ:: እሰከነ ትገብእ ድኅረ በትህዛዘ ክርስቶስ መሢሕ:: ሀብተ ማርያም ርግብ ሀብተ ማርያም የዋህ:: አብሥረኒ ብሥራተ ጽድቅ ከመ ብሥራተ አብ ኖኅ::በኂሩተ አምላክ ባዕል ወአኮ በፍትሕ::
🌸ከአሁን በፊት ከሰማይ በታች ያልተሰማ የሚያስደንቅ ነገር በ ደብረ ሊባኖስ ውስጥ ተሰማ በደልን ሁሉ በአማላጅነቱ የሚያስተሰርይ የአባታችን የአቡነ ሀብተማርያምን ድንቅ ስራን የባህር ውሃ መስክራለችና የጻድቁ አባታችን የአቡነ ሀብተማርያም አምላክ እንዲሁም የሁላችን አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ እኛን ልጆችህን ከመከራ ስጋ ከመከራ ነፍስ ሰውረን ከዳቢሎስ ውጊያም ለዘለዓለሙ ጠብቀን ::
🌺ጻዲቁ አቡነ ሀብተማርያም በፈሪሃ እግዚአብሔር በትምህርት አደገ፡፡ ከዕለታት በአንድ ቀን ካህናቱ በቤተክርስቲያን ምህላ ሲያደርሱ "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" እያሉ ሲፀልዩ ሰምቶ በልቡናው ይህች ፀሎት በጣም ጥሩና መልካም ፀሎት ናት አለ በዚህ ፀሎት ከዓለም አሳችነት ከገሃነም እሳት እንድንባት ዘንድ አውቃለሁ የንስሐ መንገድ ናት ብሎ ተናገረ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም በዚህች ፀሎት ተጠምዶ በጾምና በፀሎት በስደት የሚኖር ሆነ::
🌻አምላከ አቡነ ሀብተማርያም ሆይ እኛን ሁላችንን ከተቃጣ መዓት ከታዘዘ መቅሰፍት ከድንገተኛ ሞት ሰውረን ለዘለዓለሙ አሜን::
(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)
🌹ትክበር ነፍስየ በቅድሜከ ዮም
🌹ባርከኒ አባ(5) ሀብተማርያም😇
🌼የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን ::
🌷ሰላም ለጻአተ ነፍሰከ እምቤተ ሥጋሃ ንጽሕ:: እሰከነ ትገብእ ድኅረ በትህዛዘ ክርስቶስ መሢሕ:: ሀብተ ማርያም ርግብ ሀብተ ማርያም የዋህ:: አብሥረኒ ብሥራተ ጽድቅ ከመ ብሥራተ አብ ኖኅ::በኂሩተ አምላክ ባዕል ወአኮ በፍትሕ::
🌸ከአሁን በፊት ከሰማይ በታች ያልተሰማ የሚያስደንቅ ነገር በ ደብረ ሊባኖስ ውስጥ ተሰማ በደልን ሁሉ በአማላጅነቱ የሚያስተሰርይ የአባታችን የአቡነ ሀብተማርያምን ድንቅ ስራን የባህር ውሃ መስክራለችና የጻድቁ አባታችን የአቡነ ሀብተማርያም አምላክ እንዲሁም የሁላችን አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ እኛን ልጆችህን ከመከራ ስጋ ከመከራ ነፍስ ሰውረን ከዳቢሎስ ውጊያም ለዘለዓለሙ ጠብቀን ::
🌺ጻዲቁ አቡነ ሀብተማርያም በፈሪሃ እግዚአብሔር በትምህርት አደገ፡፡ ከዕለታት በአንድ ቀን ካህናቱ በቤተክርስቲያን ምህላ ሲያደርሱ "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" እያሉ ሲፀልዩ ሰምቶ በልቡናው ይህች ፀሎት በጣም ጥሩና መልካም ፀሎት ናት አለ በዚህ ፀሎት ከዓለም አሳችነት ከገሃነም እሳት እንድንባት ዘንድ አውቃለሁ የንስሐ መንገድ ናት ብሎ ተናገረ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም በዚህች ፀሎት ተጠምዶ በጾምና በፀሎት በስደት የሚኖር ሆነ::
🌻አምላከ አቡነ ሀብተማርያም ሆይ እኛን ሁላችንን ከተቃጣ መዓት ከታዘዘ መቅሰፍት ከድንገተኛ ሞት ሰውረን ለዘለዓለሙ አሜን::
(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)
🌹ትክበር ነፍስየ በቅድሜከ ዮም
🌹ባርከኒ አባ(5) ሀብተማርያም😇
January 4, 2020
🔔የ ተወደዳችሁ የጻድቁ ልጆች ማንኛውንም አስተያየቶች እና የጻድቁ አቡነ ሀብተማርያም ስዕል የ ገዳማቱን ፎቶግራፍ ያላችሁ በውስጥ @yordanos_26 ትልኩልን ዘንድ እንጠይቃለን @yordanos_26
January 5, 2020
ጻድቁ አቡነ ሀብተ ማርያም pinned «🔔የ ተወደዳችሁ የጻድቁ ልጆች ማንኛውንም አስተያየቶች እና የጻድቁ አቡነ ሀብተማርያም ስዕል የ ገዳማቱን ፎቶግራፍ ያላችሁ በውስጥ @yordanos_26 ትልኩልን ዘንድ እንጠይቃለን @yordanos_26»
የአቡነ ሀብተ ማርያም ተአምር
ልመናውና ክብሩ ጸሎቱና በረከቱ ከመላው ህዝበ ክርስቲያን ለዘላለም በእውነት ይደርብንና አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም ያደረገው ተአምር ይህ ነው፡፡
ፈቃደ ሥጋው አልፈጸምለት እያለ በዚህ ዓለም እያዘነ፣ እየተከዘ የሚኖር አንድ ሰው ነበር፡፡
ከዕለታት በአንዱ ቀን ከአባታችን ከአቡነ ሐብተ ማርያም ብዙህ ሰዎች ሲመጡ አገኘ፡፡ አባቶቼ ወንድሞቼ እንደምን ዋላችሁ ብሎ ያ ሰው ሰላምታ ከሰጣቸው በኋላ ከወዴት ትመጣላችሁ ብሎ ቢጠይቃቸው
ከአባታችን ከአቡነ ሀብተ ማርያም ገዳም ነው የመጣነው አሉት፣ አቡነ ሀብተ ማርያም የልባቸውን አሳብ የቤታቸውን ኃዘን ኣሟልቶ እንደሠራላቸው ነገሩት፣ እኔም ለአባታችን ለአቡነ ሃብተ ማርያም የልቤን ብነግረው፣ ይፈጽምልኛልን አላቸው፤ አዎን ይፈጽምልሃል ቢሉት፤
ከዚህ በኋላ አባቴ አቡነ ሀብተ ማርያም አንተ የልቡናዬን ኃዘን ታውቃለህና የልቡናዬን ኀዘን ሰምተህ የምወደውን ነገር ብትሰጠኝ እኔም እስከ እከተ ሞቴ ዝክርህን እዘክራለሁ ብሎ በተሳለ ጊዜ፤
እንዲህም ብሎ በንጹሕ ልቡና በለመነ ጊዜ
አባታችን አቡነ ሐብተ ማርያምም ከፈጣሪው ምሕረቱን አምኖ ያ ሰው አዝኖ ተክዞ የለመነውን የልቡናን አሳብ ሁሉ አደረገለት ፈፀመለት
በተፈፀመለት ጊዜ ፈጽሞ ደስ እንዳለው አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም እንደዚሁ የኛንም የልባችንን ኀዘን ፈጽሞ ደስ ያሰኘን፡፡ ይህን ያደረገ የአባታችን ልመናውና ክብሩ ጸሎቱና በረከቱ ለዘላለም በእውነት ይደርብን ዛሬም ዘወትርም ለዘለአለም አሜን፡፡
ልመናውና ክብሩ ጸሎቱና በረከቱ ከመላው ህዝበ ክርስቲያን ለዘላለም በእውነት ይደርብንና አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም ያደረገው ተአምር ይህ ነው፡፡
ፈቃደ ሥጋው አልፈጸምለት እያለ በዚህ ዓለም እያዘነ፣ እየተከዘ የሚኖር አንድ ሰው ነበር፡፡
ከዕለታት በአንዱ ቀን ከአባታችን ከአቡነ ሐብተ ማርያም ብዙህ ሰዎች ሲመጡ አገኘ፡፡ አባቶቼ ወንድሞቼ እንደምን ዋላችሁ ብሎ ያ ሰው ሰላምታ ከሰጣቸው በኋላ ከወዴት ትመጣላችሁ ብሎ ቢጠይቃቸው
ከአባታችን ከአቡነ ሀብተ ማርያም ገዳም ነው የመጣነው አሉት፣ አቡነ ሀብተ ማርያም የልባቸውን አሳብ የቤታቸውን ኃዘን ኣሟልቶ እንደሠራላቸው ነገሩት፣ እኔም ለአባታችን ለአቡነ ሃብተ ማርያም የልቤን ብነግረው፣ ይፈጽምልኛልን አላቸው፤ አዎን ይፈጽምልሃል ቢሉት፤
ከዚህ በኋላ አባቴ አቡነ ሀብተ ማርያም አንተ የልቡናዬን ኃዘን ታውቃለህና የልቡናዬን ኀዘን ሰምተህ የምወደውን ነገር ብትሰጠኝ እኔም እስከ እከተ ሞቴ ዝክርህን እዘክራለሁ ብሎ በተሳለ ጊዜ፤
እንዲህም ብሎ በንጹሕ ልቡና በለመነ ጊዜ
አባታችን አቡነ ሐብተ ማርያምም ከፈጣሪው ምሕረቱን አምኖ ያ ሰው አዝኖ ተክዞ የለመነውን የልቡናን አሳብ ሁሉ አደረገለት ፈፀመለት
በተፈፀመለት ጊዜ ፈጽሞ ደስ እንዳለው አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም እንደዚሁ የኛንም የልባችንን ኀዘን ፈጽሞ ደስ ያሰኘን፡፡ ይህን ያደረገ የአባታችን ልመናውና ክብሩ ጸሎቱና በረከቱ ለዘላለም በእውነት ይደርብን ዛሬም ዘወትርም ለዘለአለም አሜን፡፡
"ቅዱሳን በዓለም ላይ እንደሚፈርዱ አታውቁምን?" 1ቆሮ6:2
"Or do you not know that the saints will judge the world?"
“❤️ፍቅር ያገብረኒ ነጊረ ዜናሆሙ ለቅዱሳን❤️” አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
🙇♀️የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን ::
🙇♀️አምላከ አቡነ ሀብተማርያም ሆይ እኛን ሁላችንን ከተቃጣ መዓት ከታዘዘ መቅሰፍት ከድንገተኛ ሞት ሰውረን ለዘለዓለሙ አሜን::
(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያ
"Or do you not know that the saints will judge the world?"
“❤️ፍቅር ያገብረኒ ነጊረ ዜናሆሙ ለቅዱሳን❤️” አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
🙇♀️የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን ::
🙇♀️አምላከ አቡነ ሀብተማርያም ሆይ እኛን ሁላችንን ከተቃጣ መዓት ከታዘዘ መቅሰፍት ከድንገተኛ ሞት ሰውረን ለዘለዓለሙ አሜን::
(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያ
February 4, 2020
🙇♀️ጌታችንም ለጻድቁ አቡነ ሀብተማርያም ሰባት የጽድቅ
አክሊሎችን አዘጋጅልሃለሁ ያለው ቃል ኪዳን
1. ስለ ንፁህ ድንግልናህ፣
2. አለምንና በውስጡ ያለውን ንቀህ በመኖርህ፣
3. ስለ ፍፁም ምንኩስናህ፣
4. ዘወትር አራቱን ወንጌላትን በማንበብህና በመፀለይህ፣
5. ስለ እኔ ብለህ ስለተራብከው፣
6. በጾም ስለተጋደልክ፣
7. ቂምና ጥላቻን፣ ትዕቢትን፣ ትምክህትን፣ በልብህ ውስጥ ባለማስቀመጥህ
ስለ ንፁህ ተልዕኮ ክህነትህ፣ ስለ ንፁህ መስዋዕትህ ነው ብሎ ቃል ኪዳን
ሰጠው፡፡
😇2. አቡነ ሀብተማርያም ከተሰጣቸው ቃል ኪዳኖች ውስጥ
አምስት መቅሰፍቶች የማስወገድ ስልጣን ተሰጧቸዋል፡፡ እነሱም፡-
1. መብረቅ፣
2. ቸነፈር፣
3. ረሃብ፣
4. ወረርሽኝ፣
5. የእሳት ቃጠሎ ናቸው፡፡
አክሊሎችን አዘጋጅልሃለሁ ያለው ቃል ኪዳን
1. ስለ ንፁህ ድንግልናህ፣
2. አለምንና በውስጡ ያለውን ንቀህ በመኖርህ፣
3. ስለ ፍፁም ምንኩስናህ፣
4. ዘወትር አራቱን ወንጌላትን በማንበብህና በመፀለይህ፣
5. ስለ እኔ ብለህ ስለተራብከው፣
6. በጾም ስለተጋደልክ፣
7. ቂምና ጥላቻን፣ ትዕቢትን፣ ትምክህትን፣ በልብህ ውስጥ ባለማስቀመጥህ
ስለ ንፁህ ተልዕኮ ክህነትህ፣ ስለ ንፁህ መስዋዕትህ ነው ብሎ ቃል ኪዳን
ሰጠው፡፡
😇2. አቡነ ሀብተማርያም ከተሰጣቸው ቃል ኪዳኖች ውስጥ
አምስት መቅሰፍቶች የማስወገድ ስልጣን ተሰጧቸዋል፡፡ እነሱም፡-
1. መብረቅ፣
2. ቸነፈር፣
3. ረሃብ፣
4. ወረርሽኝ፣
5. የእሳት ቃጠሎ ናቸው፡፡
“ፍቅር ያገብረኒ ነጊረ ዜናሆሙ ለቅዱሳን” አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
🔔እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም በዓል አደረሰን አደረሳችሁ አሜን፡፡
† እግዚአብሔር የቅዱሳንን ነፍስ ይጠብቃል ከሃጢአት እጅም ያድናቸዋል::† መዝ.96፡10
🌼የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን ::
🌷ኦ ሚካኤል እግዚእየ ወፍቁርየ ኢትጸመመኒ ወኢትግድፈኒ ውስተጽምዕ ወይኩን ዘአልቦ ረዳኢ::ወሶቤሃ መጽኡ ኅቤሁ 7ቱ ሊቃነ መላእክት እንዘ ሚካኤል ቅድሜሆሙ የሐውር::..."ገድለ አቡነ ሀብተ ማርያም ዘይትነበብ በዕለተ ረቡዕ
† ሰላም ለአራኅከ ነሣኤ ኅለት ዘአሚን::
ዘይትባሕዩ ቦቱ አባግዒከ ዝርዋን::
ሀብተ ማርያም መርስ ሀብተ ማርያም ዛኅን::
ይሱቀኒ እምትንታኔ ጸሎትከ በትረ ሐፂን::
ለቁረተ ነፍስየ ካዕበ ቃልከ ክዳን::
🤲በአለም የተበተኑ በጏች የተባሉ ልጆችህ የሚጠበቅበት የእምነት ዘንግን ለጨበጠ መሐል እጅህ ሰላምታ ይገባል::ጻድቁ አባቴ ሀብተማርያም ሆይ የዚች አለም ጸጥታዋና ሰላሟ አንተ ነህ እኮ እኔን ለመውደቅ የተፍገመገምኩትን እንደብረት ዘንግ የሆነ ጸሎትህ ከወደቅኩበት መሬት ያንሳኝ ይደግፈኝ ሁለተኛም የጏሰቆለች ነፍሴን ቃልኪዳንህ አይለያት::(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)
"#ኢትዮጵያዊው_ፃዲቅ_አቡነ_ሀብተማርያም
➬እኒህ ጻድቅ ደግሞ የሃገራችን ኮከበ ገዳም ናቸው:: "ጽድቅና ትሩፋት እንደ ሃብተ ማርያም" እንዲሉ አበው:: ባሕር ከሆነ ጣዕመ ሕይወታቸው ጥቂቱን ለበረከት እንካፈል::
ጻድቁ መካነ ሙላዳቸው ሽዋ (የራውዕይ) ውስጥ ሲሆን አባታቸው ፍሬ ቡሩክ: እናታቸውት ደግሞ ቅድስት ዮስቴና ትባላለች:: በተለይ ቅድስት ዮስቴና እጅግ ደመ ግቡ: ምጽዋትን ወዳጅ: ቡርክት ሴት ነበረች:: እንዲያውም ከጻድቁ መወለድ በፊት መንና ጭው ካለ በርሃ ገብታ ነበር::
+ግን የበቃ ግኁስ አግኝቷት "ከማሕጸንሽ ደግ የሥላሴ ባርያ አለና ተመለሽ" ብሏት እንደ ገና ተመልሳለች:: ጻድቁን ወልዳ አሳድጋም እንደ ገና መንና በተጋድሎ ኑራ 7 አክሊላትን ተቀብላ ዐርፋለች::
+ወደ ጻድቁ ዜና ሕይወት ስንመለስ አቡነ ሃብተ ማርያም ገና ሕጻን እያሉ ከእናታቸው ጋር ቆመው ሲያስቀድሱ "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" ሲባል ይሰማሉ:: ይሕችን ጸሎት በሕጻን አንደበታቸው ይዘው ሌሊት ሌሊት እየተነሱ "ማረን እባክህን?" እያሉ ይሰግዱ ነበር::
+የ5 ዓመት ሕጻን እንዲህ ሲያደርግ ማየቱ በእውነት ይደንቃል:: ትንሽ ከፍ ብለው በእረኝነት ሳሉም ፍጹም ተሐራሚና ጸዋሚ ነበሩ:: ጸጋው ስለ በዛላቸውም ልጅ ሆነው ብዙ ተአምራትን ሰርተዋል:: የፈጣሪውን ስም ያቃለውን አንድ እረኛም በዓየር ላይ ሰቅለው አውለውታል::
+ከዚያ ግን ለአካለ መጠን ሲደርሱ ወደ ት/ቤት ገብተው: መጻሕፍትንም አጥንተው መንነዋል:: በአባ መልከ ጼዴቅ እጅ ከመነኮሱ በሁዋላ የሠሩትን ትሩፋትና የነበራቸውን ተጋድሎ ግን የኔ ብጤ ደካማ ሰው ሊዘረዝረው አይችልም::
*ባሕር ውስጥ ሰጥመው 500 ጊዜ ይሰግዳሉ::
*በየቀኑ 4ቱን ወንጌልና 150 መዝሙረ ዳዊትን ይጸልያሉ:: (መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ታላቅ ጸሎት ነው)
*በ40 ቀናት: ቀጥሎም በ80 ቀን አንዴ ብቻ ይመገባሉ::
*ምግባቸው ደግሞ ሣርና ቅጠል ብቻ ነው::
*በየዕለቱ ያለ ማስታጐል ማዕጠንት ያሳርጋሉ:: (ካህን ናቸውና)
*ዘወትር በንጽሕና ቅዱስ ሥጋውን ይበላሉ: ክቡር ደሙን ይጠጣሉ::
*በፍጹም በልባቸው ውስጥ ቂምን: መከፋትን አላሳደሩም::
+በእነዚህና በሌሎች ትሩፋቶቻቸው ደስ የተሰኘ ጌታም ለጻድቁ የእሳትና የብርሃን ሠረገላን ሰጥቷቸው በዚያ እየበረሩ ኢየሩሳሌም ይሔዱ ነበር:: ከብዙ የተጋድሎ ዘመናት በሁዋላም የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ አዕላፍ መላእክትን አስከተትሎ መጥቶ አላቸው::
+"*ስለ እኔ ረሃብና ጥምን ስለ ታገስክ: *ስለ ምናኔሕ: *ስለ ተባረከ ምንኩስናህ: *ስለ ንጹሕ ድንግልናህ: *ቂምና በቀልን ስላለመያዝህ: *ስለ ንጹሕ ክህነትህና ማዕጠንትህ: *ቅዱስ ወንጌልን በፍቅር ስለ ማንበብህ 7 አክሊላትን እሰጥሃለሁ::"
+"በሰማይም ከመጥምቁ ዮሐንስ ጐን: 500 የእንቁ ምሰሶዎች ያሉበትን አዳራሽ ሰጥቼሃለሁ:: በስምህ የሚለምኑ: በቃል ኪዳንህ የሚማጸኑትንም ሁሉ እንድምርልህ 'አማንየ! በርእስየ!' ብዬሃለሁ" አላቸው::
+ቅዱሳን መላእክትም "ሃብተ ማርያም ወንድማችን" ሲሉ አቀፏቸው:: ጌታ ግን በዚያች ሰዓት አንድም ሦስትም ሆኖ ታያቸውና አቅፎ 3 ጊዜ ፨ይህን የተመለከቱ የናግራን ክርስቲያኖች ግን ስለ መፍራት ፈንታ በፈቃዳቸው እየተሯሯጡ ወደ እሳትና ሰይፍ ተሽቀዳደሙ::
+ከተማዋም እየነደደችና ደም እየፈሰሰባት ለ40 ቀናት ቆየች:: ይሕንን የሰማው ቅዱሱ አፄ ካሌብም ደርሶ የተረፉትን ሲታደግ ፊንሐስን ከነ ወታደሮቹ አጥፍቶታል::
🤲አምላከ አበው ወሰማዕት ጣዕመ ፍቅራቸውን: ክብራቸውን: ጸጋ በረከታቸውንም ይክፈለን::"
😇"#ዘይእዜ ቅኔ:- ቀደምተአቡሃ ለዳኖስ ዘኢትዮጵያ በሀገረታይዋን ሕያወ ወአርሞንኤም ብሔርከ። እምዝኒ መንገለዝኒ እንዘትብል በደብረታይዋን ይትቀደስ ስምከ። ነግደነግደአዳም ወሔዋን አምጣነበገዳም ዘሰበከ። ሀብተማርያም ጻድቅ ለዘአስተብረከ።ከመከመዛቲ ትገብር ዜናሀብተማርያም አቡከ።ሀብተማርያም ጻድቅ ለዘአስተብረከ።"😍
🤲ኦ አምላከ አቡነ ሀብተ ማርያም ዕቀቦ ወአድኅኖ ወባልሆ እመከራ ሥጋ ወነፍስ ወእምኩሉ ተቃራኒ ወእምኩልነ ክቡር ሀብተ ማርያም ለዓለም ዓለም አሜን ለይኩን ለይኩን::
🔔እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም በዓል አደረሰን አደረሳችሁ አሜን፡፡
† እግዚአብሔር የቅዱሳንን ነፍስ ይጠብቃል ከሃጢአት እጅም ያድናቸዋል::† መዝ.96፡10
🌼የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን ::
🌷ኦ ሚካኤል እግዚእየ ወፍቁርየ ኢትጸመመኒ ወኢትግድፈኒ ውስተጽምዕ ወይኩን ዘአልቦ ረዳኢ::ወሶቤሃ መጽኡ ኅቤሁ 7ቱ ሊቃነ መላእክት እንዘ ሚካኤል ቅድሜሆሙ የሐውር::..."ገድለ አቡነ ሀብተ ማርያም ዘይትነበብ በዕለተ ረቡዕ
† ሰላም ለአራኅከ ነሣኤ ኅለት ዘአሚን::
ዘይትባሕዩ ቦቱ አባግዒከ ዝርዋን::
ሀብተ ማርያም መርስ ሀብተ ማርያም ዛኅን::
ይሱቀኒ እምትንታኔ ጸሎትከ በትረ ሐፂን::
ለቁረተ ነፍስየ ካዕበ ቃልከ ክዳን::
🤲በአለም የተበተኑ በጏች የተባሉ ልጆችህ የሚጠበቅበት የእምነት ዘንግን ለጨበጠ መሐል እጅህ ሰላምታ ይገባል::ጻድቁ አባቴ ሀብተማርያም ሆይ የዚች አለም ጸጥታዋና ሰላሟ አንተ ነህ እኮ እኔን ለመውደቅ የተፍገመገምኩትን እንደብረት ዘንግ የሆነ ጸሎትህ ከወደቅኩበት መሬት ያንሳኝ ይደግፈኝ ሁለተኛም የጏሰቆለች ነፍሴን ቃልኪዳንህ አይለያት::(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)
"#ኢትዮጵያዊው_ፃዲቅ_አቡነ_ሀብተማርያም
➬እኒህ ጻድቅ ደግሞ የሃገራችን ኮከበ ገዳም ናቸው:: "ጽድቅና ትሩፋት እንደ ሃብተ ማርያም" እንዲሉ አበው:: ባሕር ከሆነ ጣዕመ ሕይወታቸው ጥቂቱን ለበረከት እንካፈል::
ጻድቁ መካነ ሙላዳቸው ሽዋ (የራውዕይ) ውስጥ ሲሆን አባታቸው ፍሬ ቡሩክ: እናታቸውት ደግሞ ቅድስት ዮስቴና ትባላለች:: በተለይ ቅድስት ዮስቴና እጅግ ደመ ግቡ: ምጽዋትን ወዳጅ: ቡርክት ሴት ነበረች:: እንዲያውም ከጻድቁ መወለድ በፊት መንና ጭው ካለ በርሃ ገብታ ነበር::
+ግን የበቃ ግኁስ አግኝቷት "ከማሕጸንሽ ደግ የሥላሴ ባርያ አለና ተመለሽ" ብሏት እንደ ገና ተመልሳለች:: ጻድቁን ወልዳ አሳድጋም እንደ ገና መንና በተጋድሎ ኑራ 7 አክሊላትን ተቀብላ ዐርፋለች::
+ወደ ጻድቁ ዜና ሕይወት ስንመለስ አቡነ ሃብተ ማርያም ገና ሕጻን እያሉ ከእናታቸው ጋር ቆመው ሲያስቀድሱ "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" ሲባል ይሰማሉ:: ይሕችን ጸሎት በሕጻን አንደበታቸው ይዘው ሌሊት ሌሊት እየተነሱ "ማረን እባክህን?" እያሉ ይሰግዱ ነበር::
+የ5 ዓመት ሕጻን እንዲህ ሲያደርግ ማየቱ በእውነት ይደንቃል:: ትንሽ ከፍ ብለው በእረኝነት ሳሉም ፍጹም ተሐራሚና ጸዋሚ ነበሩ:: ጸጋው ስለ በዛላቸውም ልጅ ሆነው ብዙ ተአምራትን ሰርተዋል:: የፈጣሪውን ስም ያቃለውን አንድ እረኛም በዓየር ላይ ሰቅለው አውለውታል::
+ከዚያ ግን ለአካለ መጠን ሲደርሱ ወደ ት/ቤት ገብተው: መጻሕፍትንም አጥንተው መንነዋል:: በአባ መልከ ጼዴቅ እጅ ከመነኮሱ በሁዋላ የሠሩትን ትሩፋትና የነበራቸውን ተጋድሎ ግን የኔ ብጤ ደካማ ሰው ሊዘረዝረው አይችልም::
*ባሕር ውስጥ ሰጥመው 500 ጊዜ ይሰግዳሉ::
*በየቀኑ 4ቱን ወንጌልና 150 መዝሙረ ዳዊትን ይጸልያሉ:: (መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ታላቅ ጸሎት ነው)
*በ40 ቀናት: ቀጥሎም በ80 ቀን አንዴ ብቻ ይመገባሉ::
*ምግባቸው ደግሞ ሣርና ቅጠል ብቻ ነው::
*በየዕለቱ ያለ ማስታጐል ማዕጠንት ያሳርጋሉ:: (ካህን ናቸውና)
*ዘወትር በንጽሕና ቅዱስ ሥጋውን ይበላሉ: ክቡር ደሙን ይጠጣሉ::
*በፍጹም በልባቸው ውስጥ ቂምን: መከፋትን አላሳደሩም::
+በእነዚህና በሌሎች ትሩፋቶቻቸው ደስ የተሰኘ ጌታም ለጻድቁ የእሳትና የብርሃን ሠረገላን ሰጥቷቸው በዚያ እየበረሩ ኢየሩሳሌም ይሔዱ ነበር:: ከብዙ የተጋድሎ ዘመናት በሁዋላም የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ አዕላፍ መላእክትን አስከተትሎ መጥቶ አላቸው::
+"*ስለ እኔ ረሃብና ጥምን ስለ ታገስክ: *ስለ ምናኔሕ: *ስለ ተባረከ ምንኩስናህ: *ስለ ንጹሕ ድንግልናህ: *ቂምና በቀልን ስላለመያዝህ: *ስለ ንጹሕ ክህነትህና ማዕጠንትህ: *ቅዱስ ወንጌልን በፍቅር ስለ ማንበብህ 7 አክሊላትን እሰጥሃለሁ::"
+"በሰማይም ከመጥምቁ ዮሐንስ ጐን: 500 የእንቁ ምሰሶዎች ያሉበትን አዳራሽ ሰጥቼሃለሁ:: በስምህ የሚለምኑ: በቃል ኪዳንህ የሚማጸኑትንም ሁሉ እንድምርልህ 'አማንየ! በርእስየ!' ብዬሃለሁ" አላቸው::
+ቅዱሳን መላእክትም "ሃብተ ማርያም ወንድማችን" ሲሉ አቀፏቸው:: ጌታ ግን በዚያች ሰዓት አንድም ሦስትም ሆኖ ታያቸውና አቅፎ 3 ጊዜ ፨ይህን የተመለከቱ የናግራን ክርስቲያኖች ግን ስለ መፍራት ፈንታ በፈቃዳቸው እየተሯሯጡ ወደ እሳትና ሰይፍ ተሽቀዳደሙ::
+ከተማዋም እየነደደችና ደም እየፈሰሰባት ለ40 ቀናት ቆየች:: ይሕንን የሰማው ቅዱሱ አፄ ካሌብም ደርሶ የተረፉትን ሲታደግ ፊንሐስን ከነ ወታደሮቹ አጥፍቶታል::
🤲አምላከ አበው ወሰማዕት ጣዕመ ፍቅራቸውን: ክብራቸውን: ጸጋ በረከታቸውንም ይክፈለን::"
😇"#ዘይእዜ ቅኔ:- ቀደምተአቡሃ ለዳኖስ ዘኢትዮጵያ በሀገረታይዋን ሕያወ ወአርሞንኤም ብሔርከ። እምዝኒ መንገለዝኒ እንዘትብል በደብረታይዋን ይትቀደስ ስምከ። ነግደነግደአዳም ወሔዋን አምጣነበገዳም ዘሰበከ። ሀብተማርያም ጻድቅ ለዘአስተብረከ።ከመከመዛቲ ትገብር ዜናሀብተማርያም አቡከ።ሀብተማርያም ጻድቅ ለዘአስተብረከ።"😍
🤲ኦ አምላከ አቡነ ሀብተ ማርያም ዕቀቦ ወአድኅኖ ወባልሆ እመከራ ሥጋ ወነፍስ ወእምኩሉ ተቃራኒ ወእምኩልነ ክቡር ሀብተ ማርያም ለዓለም ዓለም አሜን ለይኩን ለይኩን::
March 4, 2020
🔔"ቅዱሳን በዓለም ላይ እንደሚፈርዱ አታውቁምን?" 1ቆሮ6:2
🔔🙇♀️ አቡነ ሀብተማርያም ከተሰጣቸው ቃል ኪዳኖች ውስጥ:-
አምስት መቅሰፍቶች የማስወገድ ስልጣን ተሰጧቸዋል፡፡ እነሱም፡-
1. መብረቅ፣
2. ቸነፈር፣
3. ረሃብ፣
4. ወረርሽኝ፣
5. የእሳት ቃጠሎ ናቸው::
🤲የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን ::
🙇♀️አምላከ አቡነ ሀብተማርያም ሆይ እኛን ሁላችንን ከተቃጣ መዓት ከታዘዘ መቅሰፍት ከድንገተኛ ሞት ሰውረን ለዘለዓለሙ አሜን::
(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)
🔔🙇♀️ አቡነ ሀብተማርያም ከተሰጣቸው ቃል ኪዳኖች ውስጥ:-
አምስት መቅሰፍቶች የማስወገድ ስልጣን ተሰጧቸዋል፡፡ እነሱም፡-
1. መብረቅ፣
2. ቸነፈር፣
3. ረሃብ፣
4. ወረርሽኝ፣
5. የእሳት ቃጠሎ ናቸው::
🤲የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን ::
🙇♀️አምላከ አቡነ ሀብተማርያም ሆይ እኛን ሁላችንን ከተቃጣ መዓት ከታዘዘ መቅሰፍት ከድንገተኛ ሞት ሰውረን ለዘለዓለሙ አሜን::
(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)
March 16, 2020
🥺ቆሜያለሁ🙇♀️
ቆሜያለሁ ሁሉንም አልፌ
በምልጃው ከሞት ተርፌ
ጸሎቱ ሀይል አደረገልኝ
አቡነ ሀብተ ማርያም እረዳኝ
አዝ-------------------
አበቃ ሲባይ ወድቆ ተስፋዬ
በኃዘን ብዛት ሲፈስ እንባዬ
ገብረ ህይወት መጣ ፃድቁ አባቴ
ደዌዬ ተሻረ ፀና ጉልበቴ /፪/
አዝ-------------------
የጭንቁን ዘመን እረስቻለሁ
ከሰዎች እኩል በክብር ቆሜያለሁ
እርሱ ባይቆምልኝ በእግዚአብሔር ፊት
አልቆምም ነበር ዛሬ በሕይወት
አልኖርም ነበር ዛሬ በሕይወት
አዝ-------------------
በጽድቅ ክንዱ እየደገፈ
ክፉን በምልጃው እያሳለፈ
ስለ ቃል ኪዳኑ በስሙ ታምኜ
አልጠግብም ፃቅዱን እርሱን አመስግኜ /፪/
አዝ-------------------
በደዌ ኃጥያት የተጠቃችሁ
ሞትን በጭንቀት ለጠበቃችሁ
ፃድቁን ጥሩት ይረዳችኋዋል
ካፈር ከትቢያ ያነሳችኋል
ቆሜያለሁ ሁሉንም አልፌ
በምልጃው ከሞት ተርፌ
ጸሎቱ ሀይል አደረገልኝ
አቡነ ሀብተ ማርያም እረዳኝ
አዝ-------------------
አበቃ ሲባይ ወድቆ ተስፋዬ
በኃዘን ብዛት ሲፈስ እንባዬ
ገብረ ህይወት መጣ ፃድቁ አባቴ
ደዌዬ ተሻረ ፀና ጉልበቴ /፪/
አዝ-------------------
የጭንቁን ዘመን እረስቻለሁ
ከሰዎች እኩል በክብር ቆሜያለሁ
እርሱ ባይቆምልኝ በእግዚአብሔር ፊት
አልቆምም ነበር ዛሬ በሕይወት
አልኖርም ነበር ዛሬ በሕይወት
አዝ-------------------
በጽድቅ ክንዱ እየደገፈ
ክፉን በምልጃው እያሳለፈ
ስለ ቃል ኪዳኑ በስሙ ታምኜ
አልጠግብም ፃቅዱን እርሱን አመስግኜ /፪/
አዝ-------------------
በደዌ ኃጥያት የተጠቃችሁ
ሞትን በጭንቀት ለጠበቃችሁ
ፃድቁን ጥሩት ይረዳችኋዋል
ካፈር ከትቢያ ያነሳችኋል
March 18, 2020
ጻድቁ አቡነ ሀብተ ማርያም pinned «አቡነ ሀብተማርያም ፩ – የትውልድ ታሪካቸው የቅዱስ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም ትውልድ ሀገር የራውእይ የምትባል ምስራቃዊት ሀገር ውስጥ ሲሆን የኢትዮጵያ ንጉስ እስክንድር በነገሰ በሺ አራት መቶ ሰማንያ ስድስት ዓመተ ምህረት ፍሬ ብሩክ የሚባል አንድ ሰው በዚች ሀገር ውስጥ ነበር፡፡ ይኸውም ከከበሩም ሰዎች ተለይቶ ብዙ ገንዘብ ያለው ባለጸጋ ነበር፡፡ በህጋዊ ጋብቻ ስሟ ዮስቴና የምትባል ሴት አገባ ይህችውም…»
March 20, 2020
✍በአዲስ አበባ ኮሮና ከዓለም ይጠፋ ዘንድ የዕጣን ማጠን መርሐግብር ተካሄደ!
የኮሮና በሽታ ከዓለም ይወገድ ዘንድ በአዲስ አበባ ቃዴ በመባል በሚጠራው ተራራ ላይ የሚገኘው የአቡነ ሃብተ ማርያም ገዳም ካህናት ማዕጠንት ይዘውና ምዕመናንን አስከትለው አካባቢውን አጥነዋል። በገድለ አቡነ ሃብተ ማርያም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለጻድቁ አቡነ ሃብተ ማርያም የሰጣቸው ቃል ኪዳን ይህ ነው።
አባታችን አቡነ ሀብተማርያም ዐራቱ ወንጌላት ከማንበብ ጋር ድካምና ተጋድሎ በበዛ ጊዜ ቅዱስ ሚካኤልንና ቅዱስ ገብርኤልን በቀኝና በግራ አስከትሎ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሲስ ክርስቶስ ወደ እርሱ መጥቶ በገሀድ ታየው። ጌታችንም "ወዳጄ ሀብተማርም ሆይ ሰላም ለአንተ ይሁን" ባለው ጊዜ ከፈጣሪ ግርማ የተነሳ ደንግጦ ከመሬት ወደቀና እንደ በድን ሆነ። ጌታችንም ክቡራት በሚሆኑ እጆቹ አንስቶ በፊቱ መንፈሰ ሕይወትን አሳደረበት፡፡ ጌታችንም አቡነ ሀብተማርያምን "ወዳጄ ሀብተማርያም ሆይ ድካምህና ገድልህ ሁሉ ለዘለዓለም መታሰቢያ ሊሆን በኢየሩሳሌም ሰማያዊት ተጽፎልሃል ብዬ በእውንት እነግርሀለሁ፤ ለአንተ ለወደድኩህና ለመረጥኩህ ለወዳጄ የማቲዮስንና የማርቆስን ወንጌል ባነበብክ ጊዜ ሁሉ ተጭነህ ወደ ምትሄድበት ቦታ ሁሉ የሚያደርስህ የብርሀን ሰረገላ እሰጥሀለሁ፤ እንዳንተ ላሉ በዋሻ ከሚኖሩ ከመረጥኳቸው ቅዱሳን ትገናኝ ዘንድ ወደ ምሥራቅ፣ ወደ ምዕራብ፣ ወደ ሰሜንና ወደ ደቡብ ትሄድበት ዘንድ የብርሀን ሰረገላ ሰጥቼሀለሁ። ከሰው ፊት ከተሰወሩ ባህታዊያን ጋር ኑር ዳግመኛ የሉቃስንና የዮሐንስን ወንጌል ባነበብክ ጊዜ በእነርሱ ተጭነህ ሥጋዬን ደሜን ለመቅመስ ኢየሩሳሌም ትደርስ ዘንድ የእሳት ሰረገላ ሰጥቼሀለሁ፡፡ በፀሎትህ አምኖ በጎ ሥራ ለሚሠራልህ ሁሉ በሕይወት ሳለህ ልብስህን በመስጠት ወይም ምግብ ወይም እግር በማጠብ ወይም እንጨት ሣር በማቅረብ ወይም ውኃ በመቅዳት በመርዳት ለደከሙ ሁሉ እምርልሀለሁ ብዬ ቃልኪዳን ሰጥቼሀለሁ፡፡ በሕይወቱ ሳለ ለሚሻ መልካሙን ሥራ ሁሉ አደርግለታለሁ። ከሞትም በኃላ መንግሥተ ሰማያትን አወርሰዋለሁ። በባለሟልነት እቀበላለሁ ከአንተ ጋርም ደስ እሰኘዋለሁ፡፡
አንተ ከሞትክም በኃላ ስምህን የጠራውንና ዝክርህን የዘከረውን ሁሉ "የሀብተማርያም አምላክ ሆይ ከጠላት እጅ አድነኝ" ያለኝን በሕሊና ያሰበውን በልቦና የወሰነውን እፈፅምለታለሁ። ሰውን #ከቸነፈር ከተቅማጥ እኮእሳት መቃጠል መብረቅ በረሀብ ከሞት እንዲያድን እንደ ሐዋርያት ሥልጣን ቃልኪዳን ተሰጠው፡፡ አንትን ገድልህን ቃልኪዳንህን የናቀውንና ያቃለለውን ሁሉ ፍፁም መበቀልን እበቀለዋለሁ፡፡ ወደ መከራ ቦታ አወርደዋለሁ በበጎ ሳይሆን በመዓት ዓይን እመለከተዋለሁ፡፡ ጠላቶችህን ይበቀልልህ ወዳጆችህን ይጠብቅልህ ዘንድ መልዕክተኛዬ ቅዱስ ሚካኤልም ዘወትር አይለይህ የሰጠሁህን ቃልኪዳን እንዳልነሳህ በራሴ ማልኩልህ፡፡ እንደ ወዳጄ እንደ ፊቅጦርም በእናቴ በድንግል ማርያም አተምኩህ፡፡ ፈቅጦርን ከሰማዕታት ሁሉ አብልጬ እንደወደድኩት አንተንም ከመነኮሳት ሁሉ አብልጬ ወድጄሀለሁና ይህ የሰጠሁህ ቃልኪዳኔ ለዘላለም ይሁንልህ፡፡
በዚሁ መሠረት የዘመኑን የኮሮና ወረርሽኝ በቃልኪዳናቸው ያጠፉልን ዘንድ እንማፀናቸው። ቃልኪዳናቸው፦
➖➤ ከወረርሽኝ
➖➤ ከቸነፈር
➖➤ ከረሀብ
➖➤ ከመብረቅ
➖➤ ከእሳት አደጋ ያድናልና።
በፃድቁ አባታችን በአቡነ ሀብተማርያም በቃል ኪዳናቸው ፀንተን እንድንገኝ የልዑል እግዚአብሔር ፈቃድ ይሁንልን፡፡
ምንጭ:-ተዋህዶ
የኮሮና በሽታ ከዓለም ይወገድ ዘንድ በአዲስ አበባ ቃዴ በመባል በሚጠራው ተራራ ላይ የሚገኘው የአቡነ ሃብተ ማርያም ገዳም ካህናት ማዕጠንት ይዘውና ምዕመናንን አስከትለው አካባቢውን አጥነዋል። በገድለ አቡነ ሃብተ ማርያም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለጻድቁ አቡነ ሃብተ ማርያም የሰጣቸው ቃል ኪዳን ይህ ነው።
አባታችን አቡነ ሀብተማርያም ዐራቱ ወንጌላት ከማንበብ ጋር ድካምና ተጋድሎ በበዛ ጊዜ ቅዱስ ሚካኤልንና ቅዱስ ገብርኤልን በቀኝና በግራ አስከትሎ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሲስ ክርስቶስ ወደ እርሱ መጥቶ በገሀድ ታየው። ጌታችንም "ወዳጄ ሀብተማርም ሆይ ሰላም ለአንተ ይሁን" ባለው ጊዜ ከፈጣሪ ግርማ የተነሳ ደንግጦ ከመሬት ወደቀና እንደ በድን ሆነ። ጌታችንም ክቡራት በሚሆኑ እጆቹ አንስቶ በፊቱ መንፈሰ ሕይወትን አሳደረበት፡፡ ጌታችንም አቡነ ሀብተማርያምን "ወዳጄ ሀብተማርያም ሆይ ድካምህና ገድልህ ሁሉ ለዘለዓለም መታሰቢያ ሊሆን በኢየሩሳሌም ሰማያዊት ተጽፎልሃል ብዬ በእውንት እነግርሀለሁ፤ ለአንተ ለወደድኩህና ለመረጥኩህ ለወዳጄ የማቲዮስንና የማርቆስን ወንጌል ባነበብክ ጊዜ ሁሉ ተጭነህ ወደ ምትሄድበት ቦታ ሁሉ የሚያደርስህ የብርሀን ሰረገላ እሰጥሀለሁ፤ እንዳንተ ላሉ በዋሻ ከሚኖሩ ከመረጥኳቸው ቅዱሳን ትገናኝ ዘንድ ወደ ምሥራቅ፣ ወደ ምዕራብ፣ ወደ ሰሜንና ወደ ደቡብ ትሄድበት ዘንድ የብርሀን ሰረገላ ሰጥቼሀለሁ። ከሰው ፊት ከተሰወሩ ባህታዊያን ጋር ኑር ዳግመኛ የሉቃስንና የዮሐንስን ወንጌል ባነበብክ ጊዜ በእነርሱ ተጭነህ ሥጋዬን ደሜን ለመቅመስ ኢየሩሳሌም ትደርስ ዘንድ የእሳት ሰረገላ ሰጥቼሀለሁ፡፡ በፀሎትህ አምኖ በጎ ሥራ ለሚሠራልህ ሁሉ በሕይወት ሳለህ ልብስህን በመስጠት ወይም ምግብ ወይም እግር በማጠብ ወይም እንጨት ሣር በማቅረብ ወይም ውኃ በመቅዳት በመርዳት ለደከሙ ሁሉ እምርልሀለሁ ብዬ ቃልኪዳን ሰጥቼሀለሁ፡፡ በሕይወቱ ሳለ ለሚሻ መልካሙን ሥራ ሁሉ አደርግለታለሁ። ከሞትም በኃላ መንግሥተ ሰማያትን አወርሰዋለሁ። በባለሟልነት እቀበላለሁ ከአንተ ጋርም ደስ እሰኘዋለሁ፡፡
አንተ ከሞትክም በኃላ ስምህን የጠራውንና ዝክርህን የዘከረውን ሁሉ "የሀብተማርያም አምላክ ሆይ ከጠላት እጅ አድነኝ" ያለኝን በሕሊና ያሰበውን በልቦና የወሰነውን እፈፅምለታለሁ። ሰውን #ከቸነፈር ከተቅማጥ እኮእሳት መቃጠል መብረቅ በረሀብ ከሞት እንዲያድን እንደ ሐዋርያት ሥልጣን ቃልኪዳን ተሰጠው፡፡ አንትን ገድልህን ቃልኪዳንህን የናቀውንና ያቃለለውን ሁሉ ፍፁም መበቀልን እበቀለዋለሁ፡፡ ወደ መከራ ቦታ አወርደዋለሁ በበጎ ሳይሆን በመዓት ዓይን እመለከተዋለሁ፡፡ ጠላቶችህን ይበቀልልህ ወዳጆችህን ይጠብቅልህ ዘንድ መልዕክተኛዬ ቅዱስ ሚካኤልም ዘወትር አይለይህ የሰጠሁህን ቃልኪዳን እንዳልነሳህ በራሴ ማልኩልህ፡፡ እንደ ወዳጄ እንደ ፊቅጦርም በእናቴ በድንግል ማርያም አተምኩህ፡፡ ፈቅጦርን ከሰማዕታት ሁሉ አብልጬ እንደወደድኩት አንተንም ከመነኮሳት ሁሉ አብልጬ ወድጄሀለሁና ይህ የሰጠሁህ ቃልኪዳኔ ለዘላለም ይሁንልህ፡፡
በዚሁ መሠረት የዘመኑን የኮሮና ወረርሽኝ በቃልኪዳናቸው ያጠፉልን ዘንድ እንማፀናቸው። ቃልኪዳናቸው፦
➖➤ ከወረርሽኝ
➖➤ ከቸነፈር
➖➤ ከረሀብ
➖➤ ከመብረቅ
➖➤ ከእሳት አደጋ ያድናልና።
በፃድቁ አባታችን በአቡነ ሀብተማርያም በቃል ኪዳናቸው ፀንተን እንድንገኝ የልዑል እግዚአብሔር ፈቃድ ይሁንልን፡፡
ምንጭ:-ተዋህዶ
March 21, 2020
March 23, 2020
4_6037194434293008483.pdf
3.7 MB
መልክአ አቡነ ሀብተማርያም
ስለ #ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ #ሀብተ ማርያም ታሪክ ፣ ገድል ፣ ተአምራት እና መልክዕ እንዲያገኙ ይቀላቀሉ።
ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን የጻድቁ ቤተሰብ ይሁኑ
👇👇👇👇👇👇👇
@AbuneHabtemariyamtsdik
@AbuneHabtemariyamtsdik
👆👆👆👆👆👆👆
Contact @yordanos_26
ስለ #ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ #ሀብተ ማርያም ታሪክ ፣ ገድል ፣ ተአምራት እና መልክዕ እንዲያገኙ ይቀላቀሉ።
ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን የጻድቁ ቤተሰብ ይሁኑ
👇👇👇👇👇👇👇
@AbuneHabtemariyamtsdik
@AbuneHabtemariyamtsdik
👆👆👆👆👆👆👆
Contact @yordanos_26
March 28, 2020
"በረከት በጻድቅ ሰው ራስ ላይ ነው:: የኀጥአንን አፍ ግን ግፍ ይከድነዋል:: የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው:: የኀጥአን ስም ግን ይጠፋል::" ምሳሌ ፲፥፮
🛐ፅሩይ እምወርቅ ወእምብሩርንጡፍ ወሕሩይ እምአእላፍ
ሀብተማርያም መልአክ(2)ዘውገኪሩብ
✝️ኢትዮጵያዊው ፃዲቅ አቡነ ሀብተማርያም ወር በገባ በ 26 በቤተክርስቲያናችን ታስበው ከሚውሉት እግዚአብሔር አምላክ ቃል ኪዳን ከገባላቸውን ከሰጣቸው ቅዱሳን አባቶቻችን አንዱ ኢትዮጵያዊው ጻድቅ ፃዲቅ አቡነ ሀብተማርያም ይገኛሉ ታዲያ ጻድቁ ፃዲቅ አቡነ ሀብተማርያም ማን ናቸው ? ምን ቃል ኪዳን ተሰጣቸው? እናም ያደረጉትን ተጋድሎ በጥቂቱ እንመልከት፦
አምስቱን መቅሰፍቶች የማስወገድ ስልጣን የተሰጠው ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያም የነበረበት ዘመን 1486 ዓ.ም ንጉስ እስክንድር በነገሰበት ጊዜ
ነው፡፡ አባቱ ፍሬ ቡሩክ እናቱ ዮስቴና ይባላሉ፡፡ ፍሬ ቡሩክና ዮስቴና በህገ እግዚአብሔር በሃይማኖት በትሩፋት በምግባር ፀንተው የሚኖሩ ደጋግ ክርስቲያኖች ነበሩ፡፡
የፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያም እናት ቅድስት ዮስቴና ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያምን ከመውለዷ በፊት ሰው ሁሉ ዓለሙን ቢገዛ ነፍሱን ካጣ ምን ይጠቅመዋል የሚለውን የወንጌል ቃል ተረድታ መንና ወደ በረሃ ሄደች፡፡ በበረሃ ውስጥም ከሰው ተለይቶ የሚኖር ባህታዊ በዋሻ ውስጥ አገኘች፣ የመጣሁት ለምነና ነው ጌታ በወንጌሉ እርፍን ይዞ ወደ ኋላ የሚያርስ የለም እንዳለ ወደ ዓለም አልመለሰም አለችው፡፡ ሉቃ 9፣62
ይህም ባህታዊ ምናኔ ምንኩስና ለአንቺ አልተፈቀደልሽም ከህጋዊው ባልሽ ወንድ ልጅ ትወልጃለሽ እርሱም ለዓለም ሁሉ ይተርፋል በፀሎቱም ብዙዎቹን ይጠቅማል እንደ መልአክትም ክንፈ ጸጋ ተሰጥቶታል በማለት ነገራት፡፡
ቅድስት ዮስቴናም ከአረጋዊ ባህታዊ ይህን ነገር ሰምታ አደነቀች የፈጣሪዬ ፈቃድ ከሆነ ወደ ቤቴ እመለሳለሁ ብላ ወደ ቤቷ ተመለሰች፡፡ ጥቂት ጊዜያት ከቆየች በኋላ ግንቦት 26 ቀን ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያም ተወለደ፡፡ በአባቱና በእናቱ ቤት ታላቅ ደስታ ሆነ 40 ቀን በሞላው ጊዜ በኦሪትና በሉቃስ ወንጌል እንደተፃፈ በእግዚአብሔር ፊት ያቆሙት ዘንድ ወደ ቤተክርስቲያን ወሰዱት በተጠመቀ ዕለትም ሀብተማርያም ተብሎ ተሰየመ፡፡
ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያም በፈሪሃ እግዚአብሔር በትምህርት አደገ፡፡ ከዕለታት በአንድ ቀን ካህናቱ በቤተክርስቲያን ምህላ ሲያደርሱ "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" እያሉ ሲፀልዩ ሰምቶ በልቡናው ይህች ፀሎት በጣም ጥሩና መልካም ፀሎት ናት አለ በዚህ ፀሎት ከዓለም አሳችነት ከገሃነም እሳት እንድንባት ዘንድ አውቃለሁ የንስሐ መንገድ ናት ብሎ ተናገረ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም በዚህች ፀሎት ተጠምዶ በጾምና በፀሎት በስደት የሚኖር ሆነ፡፡
አባቱ ፍሬ ብሩክ አቡነ ሀብተማርያምን የበግ ጠባቂ አደረገው እግዚአብሔር ግን በኋላ ለብዙዎች ስውራን ቅዱሳንና በዓለም ለሚኖሩ ምዕመናን በጎች ጠባቂ ያደርገው ዘንድ ወዶ መርጦታልና ያ ቀን እስኪደርስ ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ አቡነ ሀብተማርያምን ይጠብቀው ነበር፡፡ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም ከአባቱ አጠገብ ተኝቶ ሳለ ‹‹ሀብተማርያም ሀብተማርያም›› የሚል ድምጽ በሌሊት ከሰማይ መጣ፡፡ አባቱ በአጠገቡ ተኝቶ ስለነበረ የጠራው መስሎት አባቴ ሆይ አለሁ ሲል መለሰ ከዚህ በፊት ቃል ከሰማይ ጠርቶት አያውቅም ነበርና እንደ ሳሙኤል ጌታዬ ባሪያህ ይሰማሃል ተናገር አለ፡፡ ሳሙ3፤3 ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም አናገረው፡፡
ከዚህም በኋላ አባቱ ከሀገሪቱ ታላላቅ ሰዎች አንዷን እጮኛ አጨለትና ታገባለህ አለው አባታችን አቡነ ሀብተማርያም አባቴ ሆይ እኔ ራሴን ለክርስቶስ በድንግልና ለመኖር አጭቻለሁ ተራክቦዬም ቃለ ወንጌልን መስማት እንጂ ሌላ አይደለምና ለምን እንዲህ ትለኛለህ አለ፡፡ አባቱም ያለ አቡነ ሀብተማርያም ፈቃድ ሙሽራይቱን ለማምጣት ሄደ፡፡ አባታችን አቡነ ሀብተማርያምም ሀገር ጥሎ ለመሰደድ ከቤት ተደብቆ ወጣ፡፡ መንፈስ ቅዱስም በመብረቅ አምሳል አባቱን ገሰፀው በዚህ ድንጋጤ ምክንያት የስጋ አባቱ ከዚህ ኃላፊ ዓለም አረፈ፡፡ አባታችን አቡነ ሀብተማርያምም የአባቱን እረፍት ሳያይ አፋር ወደምትባል ሀገር ወደ አሰቦት አቡነ ሳሙኤል ገዳም ሄደ አባ ሳሙኤል ከሚባሉ ደግ መነኩሴ ቦታ ገብቶ ኖረ፡፡ በዚያም ገዳም ውሃ በመቅዳት እንጨት በመስበር፣ ልብስ በማጠብ እህል በመፍጨት አበው መነኮሳትን ሲያገለግል ኖረ፡፡ በአባታችን ላይ መነኮሳት ተቆጥተው ሲነሱ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በገሃድ ተገልፃ ትገስፃቸውም ነበር፡፡
በዚህ አገልግሎት ላይ ሳለ ገዳሙ ካለበት ተራራ ላይ ወደ በረሃ ወርዶ ውሃ ቀድቶ ተሸክሞ ሲመለስ ውሃውን በእንስራ እንደተሸከመ እግሩን አደናቀፈው፡፡ የቀዳው ውሃ ሊደፋበትና እንስራውም ሊሰበርበት ሲል ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አድነኝ ትወድቅ ዘንድ አትተዋት ብሎ ፀለየ፡፡ ይህን ብሎ በተናገረ ጊዜ የውሃዋ እንስራ ሳትወድቅ ቆመች እጅም ሳይነካት ተመልሳ በትከሻው ላይ ተቀመጠች አባ ሳሙኤልም ይከተሉት ነበርና ይህን ጽኑ ተዓምር አይተው አደነቁ፡፡ ማር 9፡23
እንዲሁ ከዕለታት በአንድ ቀን በሌሊት መብራት ለአባ ሳሙኤል እያበራ ሳለ መብራቱ ከእጁ ወድቆ ጠፋ፡፡ ስለ መምህሩ ስለ አባ ሳሙኤል ቁጣ፣ ፍራቻ፣ ታላቅ ድንጋጤ ደንግጦ ፈጥኖ ባነሳው ጊዜ በእግዚአብሔር ተዓምር ራሱ በራ፡፡ አባ ሳሙኤልም ይህን ተዓምራት አይተው የዚህ ቅዱስ ልጅ የዓለም ሁሉ የጥበብ መብራት ይሆናል ሲሉ ትንቢት ተናገሩ፡፡ በዚህችም ገዳም 12 ዓመት ከትህትና ጋር እየታዘዘ ቤተክርስቲያንን እያገለገለ ኖረ፡፡
ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያም ከአባ ሳሙኤል ገዳም ወጥቶ እለ አድባር ወደ ተባለ ገዳም ሄደ፡፡ ከአባ መልኬጼዴቅ እጅ የምንኩስናን ስርዓት ተቀበለ፡፡ ከዚያም በመቀጠል በጥልቅ ባህር ገብቶ 150 መዝሙረ ዳዊትና አራቱን ወንጌልና ሌሎች የፀሎት መጽሐፍትን እየፀለየ አምስት መቶ ጊዜ ይሰግድ ነበር፡፡ እህል መብላትን ትቶ እንደ በረሃ ዋልያ ቅጠል መብላት ጀመረ፡፡ አርባ ቀን የሚጾምበት ጊዜና ሰማንያ ቀንም የሚጾምበት ቀን ነበር፡፡ ቅጠልም ቢሆን እህል ቀዝቃዛ ወይም ምንም አይቀምስም ነበር፡፡ ፊቱም እንደ ንጋት ኮከብ ያበራ ነበር፡፡
አራቱን ወንጌላት እየፀለየ ሳለ ቅዱስ ገብርኤልንና ቅዱስ ሚካኤልን በቀኝና በግራ አስከትሎ ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጠለት፡፡ ወዳጄ ሀብተማርያም ሆይ ሰላም ላንተ ይሁን አለው ያን ጊዜ አቡነ ሀብተማርያም ከፈጣሪው ግርማ የተነሳ ደንግጦ ከመሬት ወድቆ እንደ በድን ሆነ፡፡ ጌታችንም አንስቶ ክቡራን በሆኑ እጆቹ አፀናው ታላቅ የሆነ ቃል ኪዳንም ገባለት በፀሎትህ አምኖ በጎ ስራ ለሚሰራ ሁሉ በህይወት ሳለህ ልብስ በመስጠት ወይም ምግብ በማቅረብ፣ እግር በማጠብ፣ እንጨት ሳር በማቅረብ፣ ውሃ በመቅዳትና በመርዳት ለደከመ ሁሉ እምርልሃለሁ ዳግመኛ ከሞተ በኋላ መንግስተ ሰማያትን አወርሰዋለሁ አንተ ከሞትክም በኋላ ስምህን የጠራውን ዝክርህን ያዘከረውን ሁሉ የሀብተማርያም አምላክ ሆይ ከጠላት እጅ አድነኝ ያለኝን በህሊና ያሰበውን በልቦናው የወሰነውን እፈጽምለታለሁ አለው፡፡ ማቴ 10፡41-42
🛐ፅሩይ እምወርቅ ወእምብሩርንጡፍ ወሕሩይ እምአእላፍ
ሀብተማርያም መልአክ(2)ዘውገኪሩብ
✝️ኢትዮጵያዊው ፃዲቅ አቡነ ሀብተማርያም ወር በገባ በ 26 በቤተክርስቲያናችን ታስበው ከሚውሉት እግዚአብሔር አምላክ ቃል ኪዳን ከገባላቸውን ከሰጣቸው ቅዱሳን አባቶቻችን አንዱ ኢትዮጵያዊው ጻድቅ ፃዲቅ አቡነ ሀብተማርያም ይገኛሉ ታዲያ ጻድቁ ፃዲቅ አቡነ ሀብተማርያም ማን ናቸው ? ምን ቃል ኪዳን ተሰጣቸው? እናም ያደረጉትን ተጋድሎ በጥቂቱ እንመልከት፦
አምስቱን መቅሰፍቶች የማስወገድ ስልጣን የተሰጠው ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያም የነበረበት ዘመን 1486 ዓ.ም ንጉስ እስክንድር በነገሰበት ጊዜ
ነው፡፡ አባቱ ፍሬ ቡሩክ እናቱ ዮስቴና ይባላሉ፡፡ ፍሬ ቡሩክና ዮስቴና በህገ እግዚአብሔር በሃይማኖት በትሩፋት በምግባር ፀንተው የሚኖሩ ደጋግ ክርስቲያኖች ነበሩ፡፡
የፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያም እናት ቅድስት ዮስቴና ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያምን ከመውለዷ በፊት ሰው ሁሉ ዓለሙን ቢገዛ ነፍሱን ካጣ ምን ይጠቅመዋል የሚለውን የወንጌል ቃል ተረድታ መንና ወደ በረሃ ሄደች፡፡ በበረሃ ውስጥም ከሰው ተለይቶ የሚኖር ባህታዊ በዋሻ ውስጥ አገኘች፣ የመጣሁት ለምነና ነው ጌታ በወንጌሉ እርፍን ይዞ ወደ ኋላ የሚያርስ የለም እንዳለ ወደ ዓለም አልመለሰም አለችው፡፡ ሉቃ 9፣62
ይህም ባህታዊ ምናኔ ምንኩስና ለአንቺ አልተፈቀደልሽም ከህጋዊው ባልሽ ወንድ ልጅ ትወልጃለሽ እርሱም ለዓለም ሁሉ ይተርፋል በፀሎቱም ብዙዎቹን ይጠቅማል እንደ መልአክትም ክንፈ ጸጋ ተሰጥቶታል በማለት ነገራት፡፡
ቅድስት ዮስቴናም ከአረጋዊ ባህታዊ ይህን ነገር ሰምታ አደነቀች የፈጣሪዬ ፈቃድ ከሆነ ወደ ቤቴ እመለሳለሁ ብላ ወደ ቤቷ ተመለሰች፡፡ ጥቂት ጊዜያት ከቆየች በኋላ ግንቦት 26 ቀን ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያም ተወለደ፡፡ በአባቱና በእናቱ ቤት ታላቅ ደስታ ሆነ 40 ቀን በሞላው ጊዜ በኦሪትና በሉቃስ ወንጌል እንደተፃፈ በእግዚአብሔር ፊት ያቆሙት ዘንድ ወደ ቤተክርስቲያን ወሰዱት በተጠመቀ ዕለትም ሀብተማርያም ተብሎ ተሰየመ፡፡
ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያም በፈሪሃ እግዚአብሔር በትምህርት አደገ፡፡ ከዕለታት በአንድ ቀን ካህናቱ በቤተክርስቲያን ምህላ ሲያደርሱ "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" እያሉ ሲፀልዩ ሰምቶ በልቡናው ይህች ፀሎት በጣም ጥሩና መልካም ፀሎት ናት አለ በዚህ ፀሎት ከዓለም አሳችነት ከገሃነም እሳት እንድንባት ዘንድ አውቃለሁ የንስሐ መንገድ ናት ብሎ ተናገረ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም በዚህች ፀሎት ተጠምዶ በጾምና በፀሎት በስደት የሚኖር ሆነ፡፡
አባቱ ፍሬ ብሩክ አቡነ ሀብተማርያምን የበግ ጠባቂ አደረገው እግዚአብሔር ግን በኋላ ለብዙዎች ስውራን ቅዱሳንና በዓለም ለሚኖሩ ምዕመናን በጎች ጠባቂ ያደርገው ዘንድ ወዶ መርጦታልና ያ ቀን እስኪደርስ ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ አቡነ ሀብተማርያምን ይጠብቀው ነበር፡፡ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም ከአባቱ አጠገብ ተኝቶ ሳለ ‹‹ሀብተማርያም ሀብተማርያም›› የሚል ድምጽ በሌሊት ከሰማይ መጣ፡፡ አባቱ በአጠገቡ ተኝቶ ስለነበረ የጠራው መስሎት አባቴ ሆይ አለሁ ሲል መለሰ ከዚህ በፊት ቃል ከሰማይ ጠርቶት አያውቅም ነበርና እንደ ሳሙኤል ጌታዬ ባሪያህ ይሰማሃል ተናገር አለ፡፡ ሳሙ3፤3 ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም አናገረው፡፡
ከዚህም በኋላ አባቱ ከሀገሪቱ ታላላቅ ሰዎች አንዷን እጮኛ አጨለትና ታገባለህ አለው አባታችን አቡነ ሀብተማርያም አባቴ ሆይ እኔ ራሴን ለክርስቶስ በድንግልና ለመኖር አጭቻለሁ ተራክቦዬም ቃለ ወንጌልን መስማት እንጂ ሌላ አይደለምና ለምን እንዲህ ትለኛለህ አለ፡፡ አባቱም ያለ አቡነ ሀብተማርያም ፈቃድ ሙሽራይቱን ለማምጣት ሄደ፡፡ አባታችን አቡነ ሀብተማርያምም ሀገር ጥሎ ለመሰደድ ከቤት ተደብቆ ወጣ፡፡ መንፈስ ቅዱስም በመብረቅ አምሳል አባቱን ገሰፀው በዚህ ድንጋጤ ምክንያት የስጋ አባቱ ከዚህ ኃላፊ ዓለም አረፈ፡፡ አባታችን አቡነ ሀብተማርያምም የአባቱን እረፍት ሳያይ አፋር ወደምትባል ሀገር ወደ አሰቦት አቡነ ሳሙኤል ገዳም ሄደ አባ ሳሙኤል ከሚባሉ ደግ መነኩሴ ቦታ ገብቶ ኖረ፡፡ በዚያም ገዳም ውሃ በመቅዳት እንጨት በመስበር፣ ልብስ በማጠብ እህል በመፍጨት አበው መነኮሳትን ሲያገለግል ኖረ፡፡ በአባታችን ላይ መነኮሳት ተቆጥተው ሲነሱ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በገሃድ ተገልፃ ትገስፃቸውም ነበር፡፡
በዚህ አገልግሎት ላይ ሳለ ገዳሙ ካለበት ተራራ ላይ ወደ በረሃ ወርዶ ውሃ ቀድቶ ተሸክሞ ሲመለስ ውሃውን በእንስራ እንደተሸከመ እግሩን አደናቀፈው፡፡ የቀዳው ውሃ ሊደፋበትና እንስራውም ሊሰበርበት ሲል ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አድነኝ ትወድቅ ዘንድ አትተዋት ብሎ ፀለየ፡፡ ይህን ብሎ በተናገረ ጊዜ የውሃዋ እንስራ ሳትወድቅ ቆመች እጅም ሳይነካት ተመልሳ በትከሻው ላይ ተቀመጠች አባ ሳሙኤልም ይከተሉት ነበርና ይህን ጽኑ ተዓምር አይተው አደነቁ፡፡ ማር 9፡23
እንዲሁ ከዕለታት በአንድ ቀን በሌሊት መብራት ለአባ ሳሙኤል እያበራ ሳለ መብራቱ ከእጁ ወድቆ ጠፋ፡፡ ስለ መምህሩ ስለ አባ ሳሙኤል ቁጣ፣ ፍራቻ፣ ታላቅ ድንጋጤ ደንግጦ ፈጥኖ ባነሳው ጊዜ በእግዚአብሔር ተዓምር ራሱ በራ፡፡ አባ ሳሙኤልም ይህን ተዓምራት አይተው የዚህ ቅዱስ ልጅ የዓለም ሁሉ የጥበብ መብራት ይሆናል ሲሉ ትንቢት ተናገሩ፡፡ በዚህችም ገዳም 12 ዓመት ከትህትና ጋር እየታዘዘ ቤተክርስቲያንን እያገለገለ ኖረ፡፡
ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያም ከአባ ሳሙኤል ገዳም ወጥቶ እለ አድባር ወደ ተባለ ገዳም ሄደ፡፡ ከአባ መልኬጼዴቅ እጅ የምንኩስናን ስርዓት ተቀበለ፡፡ ከዚያም በመቀጠል በጥልቅ ባህር ገብቶ 150 መዝሙረ ዳዊትና አራቱን ወንጌልና ሌሎች የፀሎት መጽሐፍትን እየፀለየ አምስት መቶ ጊዜ ይሰግድ ነበር፡፡ እህል መብላትን ትቶ እንደ በረሃ ዋልያ ቅጠል መብላት ጀመረ፡፡ አርባ ቀን የሚጾምበት ጊዜና ሰማንያ ቀንም የሚጾምበት ቀን ነበር፡፡ ቅጠልም ቢሆን እህል ቀዝቃዛ ወይም ምንም አይቀምስም ነበር፡፡ ፊቱም እንደ ንጋት ኮከብ ያበራ ነበር፡፡
አራቱን ወንጌላት እየፀለየ ሳለ ቅዱስ ገብርኤልንና ቅዱስ ሚካኤልን በቀኝና በግራ አስከትሎ ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጠለት፡፡ ወዳጄ ሀብተማርያም ሆይ ሰላም ላንተ ይሁን አለው ያን ጊዜ አቡነ ሀብተማርያም ከፈጣሪው ግርማ የተነሳ ደንግጦ ከመሬት ወድቆ እንደ በድን ሆነ፡፡ ጌታችንም አንስቶ ክቡራን በሆኑ እጆቹ አፀናው ታላቅ የሆነ ቃል ኪዳንም ገባለት በፀሎትህ አምኖ በጎ ስራ ለሚሰራ ሁሉ በህይወት ሳለህ ልብስ በመስጠት ወይም ምግብ በማቅረብ፣ እግር በማጠብ፣ እንጨት ሳር በማቅረብ፣ ውሃ በመቅዳትና በመርዳት ለደከመ ሁሉ እምርልሃለሁ ዳግመኛ ከሞተ በኋላ መንግስተ ሰማያትን አወርሰዋለሁ አንተ ከሞትክም በኋላ ስምህን የጠራውን ዝክርህን ያዘከረውን ሁሉ የሀብተማርያም አምላክ ሆይ ከጠላት እጅ አድነኝ ያለኝን በህሊና ያሰበውን በልቦናው የወሰነውን እፈጽምለታለሁ አለው፡፡ ማቴ 10፡41-42
April 4, 2020
ጠላቶችህ አጋንንትን ያጠፋልህ እና ይጠብቅህ ዘንድ ቅዱስ ሚካኤል ካንተ አይለይም የሰጠሁህን ቃል ኪዳን እንዳልነሳ በራሴ ማልኩልህ ከእናትህ ማህፀን ጀምሮ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ አድርጌ መረጥኩህ እንጂ በብዙ ገድልህና በድካምህ ብቻ የወደድኩህ አይደለም፡፡ ይህን ቃል ኪዳን ከሰጠው በኋላ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በክብር፣ በብርሃን፣ በቅዳሴ፣ በስልጣን ወደ ሰማይ አረገ፡፡
ቅድስት ዮስቴናም ባሏ ከሞተ በኋላ ለራሷ ምንም ሳታስቀር ገንዘቧን እናት አባት ለሞቱባቸው፣ ለባልቴቶች፣ ለጦም አዳሪዎች፣ ለድሆች ጨርሳ ሰጠች፡፡ በጾም በፀሎትና በስግደት ሰውነቷን አደከመች፡፡ እንዲህ ባለ ገድል ሳለች ከሰማይ እንዲህ የሚል ቃል ወደ እሷ መጣ እኔን ለማገልገል ሴቶች ወንዶች ባሮችሽን፣ ወንድሞችሽን እህቶችሽን ቤትሽን ስለ ተውሽ ሰማንያ ርስት ከተሞችን ሰባት አክሊሎችን እነሆ አዘጋጀሁልሽ አላት ደጋግ ስራን ሰርታ ከፈፀመች በኋላ አረፈች፡፡ መዝ 115/116 ፡ 6 እግዚአብሔር አምላክ አስቀድሞ ተስፋውን እንደነገራት ሰባቱን አክሊላት ሸለማት ሰማንያውን አህጉራት ገነት አወረሳት፡፡
ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያም ወደ ቤተክርስቲያን በሄደ ጊዜ ወንጌል ሲነበብ የክርስቶስ ጌትነቱን የሚናገር ወንጌል ሲነበብ "ወዮሴፍ ብእሊሃ ለማርያም ፃዲቅ ውእቱ" የሚል ከቄሱ አፍ ይህን ንባብ ሲሰማ ደንግጦ ወንጌል ወደ ሚነበብበት ስፍራ ሄደ የሚያነበውን ቄስ ገሰጸው "ወዮሴፍሰ ፈሃሪሃ ለማርያም ጽድቅ ውእቱ" በል እንጂ ብእሲሃ አትበል ብሎ መከረው ቄሱም አቡነ ሀብተማርያም እንዳዘዘው ከስህተቱ ወደ ቀና ንባቡ ተመለሰ፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ተገልጾ ወዳጄ አመሰገንኩህ እናቴን ድንግል ማርያም ስለ አከበርክ እኔም በመንግስተ ሰማያት ፈጽሜ አከብርሃለሁ አለው፡፡
ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያም ከጌታ ጋር በተነጋገረ ጊዜ እንደ ነብዩ ሙሴ በፊቱ ብርሃን ተሳለ፡፡ ሰዎችም የፊቱን ብርሃን አይተው መቅረቡን ፈርተው አደነቁ፡፡ አቡነ ሀብተማርያምም ጌታ ሆይ ከንቱ ውዳሴ እንዳይሆንብኝ በፊቴ ላይ የተሳለውን ብርሃን ሰውርልኝ ብሎ ፀለየ፡፡ ጌታም ፊቱን እንደቀድሞው አደረገው፡፡ በጾም በፀሎት ላይ ሳለም በሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት ወደ ሰማይ ተነጥቆ ቅዱሳን የሚኖሩባቸውን ዓለማት መንግስተ ሰማያትንና ሲኦልን ተመለከተ፡፡
ሰይጣንም መጥቶ በእግዚአብሔር ፊት ቆመ በሀብተማርያም ላይ መከራ አፀናበት ዘንድ ፍቀድልኝ ብሎ ጮኾ፤ ተናገረ፡፡ እግዚአብሔር አምላክም በሰይጣን ላይ ተቆጥቶ በነፍሱም በስጋውም መከራ ታፀናበት ዘንድ አልፈቅድም ከእናቱ ማህፀን ጀምሮ መርጨዋለሁና በንፅህናና በቅድስና ኃጢአት እንዳይሰራ ዘወትር እጠብቀዋለሁ በእርሱ ላይ ብቻ ሳይሆን በሀብተማርያም ፀሎት በተማፀነኝ ሁሉ ላይ እንኳን አላሰለጥንህም ብሎ አሰናበተው ሰይጣንም ይህን ቃል ሰምቶ አፍሮ እያዘነ ሄደ፡፡ ያዕ 1፡12
አባታችን አቡነ ሀብተማርያም እንዲህ ባለ ስራ ላይ ሳለ ሰውነታቸው እንደ መርግድ የሚያሸበርቅ ዘጠኙ ክቡራን ሰዎች ወደ እርሱ መጡ፡፡ አብሯቸው ያለውን መልአክ ይህን ያህል ብርሃን የከበበው ይህ ሰው ማን ነው ብሎ ጠየቀው መልአኩም አባትህ ተክለሃይማኖት ነው አለው፡፡ ክቡር የሆነ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ጠርቶ ልጄ ሀብተማርያም ሆይ ፈጣሪዬ እግዚአብሔር ስለወደደህ ብዙ ምርኮ እንዳገኘህ በአንተ ፈጽሞ ደስ ይለኛል፡፡ ነገር ግን የምለምንህ ነገር አለና እሺ በለኝ አለ፡፡ አባታችን አቡነ ሀብተማርያምም ጌታዬ ነገሩ ምንድን ነው አለ? ክቡር አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖትም ከተቀበርኩበት ቦታ እንድትቀበር ቃል ኪዳን ግባልኝ አለው፡፡
✝️አቡነ ሀብተማርያምም ይህንን አደርግ ዘንድ ስለምን ትወዳለህ አለው አቡነ ተክለሃይማኖትም በሀገሬ ላይ የታዘዙ አምስት መቅሰፍቶች አሉና ነው፡፡
እነሱም፡-
1. መብረቅ፣
2. ቸነፈር፣
3. ረሃብ፣
4. ወረርሽኝ፣
5. የእሳት ቃጠሎ ናቸው፡፡
የአንተም አጽም በውስጡ የተቀበረ እንደሆነ አጥንቴ የተቀበረባት ሀገሬ ከነዚህ መቅሰፍታት ትድናለችና ልጄ ሀብተማርያም ሆይ አንተ የማታውቀው ከፈጣሪያችን ከእግዚአብሔር የተሰጠህ እኔ የማውቀው ክብር አለህና ስለዚህ ነው ቃል ኪዳን ግባልኝ ብሎ ማለደው፡፡ ይህን ሲባባሉ እንዲህ የሚል ቃል መጣ፡፡ ከወዳጄ ከሀብተማርያም አንደበት ይህ ቃል ኪዳን አይወጣም እርሱ በወደደው የሚቀበር አይደለም፡፡ እንዲህም ብለህ የምታስገድደው ለምንድን ነው እኔ በወደድሁት ቦታ ይቀበራል እንጂ የሚል ቃል ተነገረ፡፡ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖትም እየለመነና እየሰገደ ሶስት ጊዜ ከስላሴ ዙፋን ተንበረከከ፡፡ይሁን ይደረግ የሚል ቃል ከሰማይ ሰማ በወዳጄ በሀብተማርያም አጥንት ቦታህ የምትድን ስለሆነች ፈቃዴ ነው ብሎ ጌታ ቃል ኪዳን ሰጠው፡፡
ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያም በፀሎት ላይ ሳለ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ትዕዛዝ የቆምክባትን ቦታ ምስራቁን፣ ምዕራቡን፣ ሰሜኑን፣ ደቡቡን ባርክ አለው፡፡ ሲባርክም ሶስት አጋንንት በፀሎቱ ስልጣን ታስረው በፊቱ ታዩት፡፡ እነዚህም አጋንንት ከኖህ ጀምሮ ሰውን በማሳት ከኖርን በኋላ ከአንተ ጋር ምን ፀብ አለን አሉ አባታችንም አቡነ ሀብተማርያም በትዕምርተ መስቀል ሲያማትብ ሁለቱን አጋንንት ምድር ተከፍታ ዋጠቻቸው አንዱ ጊዜዬ ስላልደረሰ አታጥፋኝ አለው፡፡ ያን ጊዜ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አቡነ ሀብተማርያምን ይህንን ተወው ጊዜው አልደረሰም አለው፡፡ የጌታ ቃል እንዲህ ብሎ በተናገረ ጊዜ ሰይጣን ከአባታችን ተለይቶ ጠፋ፡፡ ማር 9፡23
ከዚህም በኋላ ዕለተ ሞቱ በደረሰ ጊዜ ለሞቱ ምክንያት የሚሆን ቸነፈር ያዘው፡፡ ጌታችንም በምስጋና ወደ እርሱ መጥቶ ወዳጄ ሀብተማርያም ሆይ ዛሬ ወደአንተ የመጣሁት ከድካም ወደ እረፍት እወስድህ ዘንድ ነው ሰባት የጽድቅ አክሊሎችን አዘጋጅልሃለሁ፡፡
1. ስለ ንፁህ ድንግልናህ፣
2. አለምንና በውስጡ ያለውን ንቀህ በመኖርህ፣
3. ስለ ፍፁም ምንኩስናህ፣
4. ዘወትር አራቱን ወንጌላትን በማንበብህና በመፀለይህ፣
5. ስለ እኔ ብለህ ስለተራብከው፣
6. በጾም ስለተጋደልክ፣
7. ቂምና ጥላቻን፣ ትዕቢትን፣ ትምክህትን፣ በልብህ ውስጥ ባለማስቀመጥህ ስለ ንፁህ ተልዕኮ ክህነትህ፣ ስለ ንፁህ መስዋዕትህ ነው ብሎ ቃል ኪዳን ሰጠው፡፡
በተጨማሪም እኔ የሰጠሁህን ቃል ኪዳን ተስፋ አድርጎ መጽሐፈ ገድልህን ለሚጽፈው ስሙን በመንግስተ ሰማያት በእውነት መጽሐፍ እጽፈዋለሁ፣ ለቤተክርስቲያንህ ዘይትን፣ ወይንን፣ ዕጣንን፣ ህብስትን እስከ ቀዝቃዛ ውሃ ድረስ በአንተ ስም መብዓ የሰጠውን የወደደውን ሁሉ አደርግለታለሁ፡፡ በመንግስተ ሰማያትም ከወዳጆቼ ከቅዱሳን ጋር በደስታ አኖረዋለሁ፡፡ የአቡነ ሀብተማርያም ፈጣሪ ኃጢአቴን ይቅር በለኝ ብሎ ያንተን ስም ጠርቶ ቢለምነኝ ኃጢአቱን አስተሰርይለታለሁ ብሎ ቃልኪዳን ገባለት ይህንንም ካለው በኋላ ጌታችን አፉን ሶስት ጊዜ ሳመው፡፡ ያን ጊዜም ከመድኃኒዓለም ጣዕም ፍቅር የተነሳ ነፍሱ ከስጋው ተለየች መዝ 115/116 ፡ 6 በሰማያዊ መልአክት በምድራውያን ስውራን ቅዱሳን ዘንድ ታላቅ ደስታ ሆነ ህዳር 26 ቀን አረፈ፡፡ ካህናት በመልካም ልብስ ገንዘው በዝማሬ በማህሌት ከቅዱስ አባታችን ከአቡነ ተክለሃይማኖት አጽም ጋር በፃዲቁ መቃብር ቀበሩት፡፡
🤲ኦ አምላከ አቡነ ሀብተ ማርያም ዕቀቦ ወአድኅኖ ወባልሆ እመከራ ሥጋ ወነፍስ ወእምኩሉ ተቃራኒ ወእምኩልነ ክቡር ሀብተ ማርያም ለዓለም ዓለም አሜን ለይኩን ለይኩን::
https://t.me/AbuneHabtemariyamtsdik
ቅድስት ዮስቴናም ባሏ ከሞተ በኋላ ለራሷ ምንም ሳታስቀር ገንዘቧን እናት አባት ለሞቱባቸው፣ ለባልቴቶች፣ ለጦም አዳሪዎች፣ ለድሆች ጨርሳ ሰጠች፡፡ በጾም በፀሎትና በስግደት ሰውነቷን አደከመች፡፡ እንዲህ ባለ ገድል ሳለች ከሰማይ እንዲህ የሚል ቃል ወደ እሷ መጣ እኔን ለማገልገል ሴቶች ወንዶች ባሮችሽን፣ ወንድሞችሽን እህቶችሽን ቤትሽን ስለ ተውሽ ሰማንያ ርስት ከተሞችን ሰባት አክሊሎችን እነሆ አዘጋጀሁልሽ አላት ደጋግ ስራን ሰርታ ከፈፀመች በኋላ አረፈች፡፡ መዝ 115/116 ፡ 6 እግዚአብሔር አምላክ አስቀድሞ ተስፋውን እንደነገራት ሰባቱን አክሊላት ሸለማት ሰማንያውን አህጉራት ገነት አወረሳት፡፡
ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያም ወደ ቤተክርስቲያን በሄደ ጊዜ ወንጌል ሲነበብ የክርስቶስ ጌትነቱን የሚናገር ወንጌል ሲነበብ "ወዮሴፍ ብእሊሃ ለማርያም ፃዲቅ ውእቱ" የሚል ከቄሱ አፍ ይህን ንባብ ሲሰማ ደንግጦ ወንጌል ወደ ሚነበብበት ስፍራ ሄደ የሚያነበውን ቄስ ገሰጸው "ወዮሴፍሰ ፈሃሪሃ ለማርያም ጽድቅ ውእቱ" በል እንጂ ብእሲሃ አትበል ብሎ መከረው ቄሱም አቡነ ሀብተማርያም እንዳዘዘው ከስህተቱ ወደ ቀና ንባቡ ተመለሰ፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ተገልጾ ወዳጄ አመሰገንኩህ እናቴን ድንግል ማርያም ስለ አከበርክ እኔም በመንግስተ ሰማያት ፈጽሜ አከብርሃለሁ አለው፡፡
ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያም ከጌታ ጋር በተነጋገረ ጊዜ እንደ ነብዩ ሙሴ በፊቱ ብርሃን ተሳለ፡፡ ሰዎችም የፊቱን ብርሃን አይተው መቅረቡን ፈርተው አደነቁ፡፡ አቡነ ሀብተማርያምም ጌታ ሆይ ከንቱ ውዳሴ እንዳይሆንብኝ በፊቴ ላይ የተሳለውን ብርሃን ሰውርልኝ ብሎ ፀለየ፡፡ ጌታም ፊቱን እንደቀድሞው አደረገው፡፡ በጾም በፀሎት ላይ ሳለም በሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት ወደ ሰማይ ተነጥቆ ቅዱሳን የሚኖሩባቸውን ዓለማት መንግስተ ሰማያትንና ሲኦልን ተመለከተ፡፡
ሰይጣንም መጥቶ በእግዚአብሔር ፊት ቆመ በሀብተማርያም ላይ መከራ አፀናበት ዘንድ ፍቀድልኝ ብሎ ጮኾ፤ ተናገረ፡፡ እግዚአብሔር አምላክም በሰይጣን ላይ ተቆጥቶ በነፍሱም በስጋውም መከራ ታፀናበት ዘንድ አልፈቅድም ከእናቱ ማህፀን ጀምሮ መርጨዋለሁና በንፅህናና በቅድስና ኃጢአት እንዳይሰራ ዘወትር እጠብቀዋለሁ በእርሱ ላይ ብቻ ሳይሆን በሀብተማርያም ፀሎት በተማፀነኝ ሁሉ ላይ እንኳን አላሰለጥንህም ብሎ አሰናበተው ሰይጣንም ይህን ቃል ሰምቶ አፍሮ እያዘነ ሄደ፡፡ ያዕ 1፡12
አባታችን አቡነ ሀብተማርያም እንዲህ ባለ ስራ ላይ ሳለ ሰውነታቸው እንደ መርግድ የሚያሸበርቅ ዘጠኙ ክቡራን ሰዎች ወደ እርሱ መጡ፡፡ አብሯቸው ያለውን መልአክ ይህን ያህል ብርሃን የከበበው ይህ ሰው ማን ነው ብሎ ጠየቀው መልአኩም አባትህ ተክለሃይማኖት ነው አለው፡፡ ክቡር የሆነ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ጠርቶ ልጄ ሀብተማርያም ሆይ ፈጣሪዬ እግዚአብሔር ስለወደደህ ብዙ ምርኮ እንዳገኘህ በአንተ ፈጽሞ ደስ ይለኛል፡፡ ነገር ግን የምለምንህ ነገር አለና እሺ በለኝ አለ፡፡ አባታችን አቡነ ሀብተማርያምም ጌታዬ ነገሩ ምንድን ነው አለ? ክቡር አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖትም ከተቀበርኩበት ቦታ እንድትቀበር ቃል ኪዳን ግባልኝ አለው፡፡
✝️አቡነ ሀብተማርያምም ይህንን አደርግ ዘንድ ስለምን ትወዳለህ አለው አቡነ ተክለሃይማኖትም በሀገሬ ላይ የታዘዙ አምስት መቅሰፍቶች አሉና ነው፡፡
እነሱም፡-
1. መብረቅ፣
2. ቸነፈር፣
3. ረሃብ፣
4. ወረርሽኝ፣
5. የእሳት ቃጠሎ ናቸው፡፡
የአንተም አጽም በውስጡ የተቀበረ እንደሆነ አጥንቴ የተቀበረባት ሀገሬ ከነዚህ መቅሰፍታት ትድናለችና ልጄ ሀብተማርያም ሆይ አንተ የማታውቀው ከፈጣሪያችን ከእግዚአብሔር የተሰጠህ እኔ የማውቀው ክብር አለህና ስለዚህ ነው ቃል ኪዳን ግባልኝ ብሎ ማለደው፡፡ ይህን ሲባባሉ እንዲህ የሚል ቃል መጣ፡፡ ከወዳጄ ከሀብተማርያም አንደበት ይህ ቃል ኪዳን አይወጣም እርሱ በወደደው የሚቀበር አይደለም፡፡ እንዲህም ብለህ የምታስገድደው ለምንድን ነው እኔ በወደድሁት ቦታ ይቀበራል እንጂ የሚል ቃል ተነገረ፡፡ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖትም እየለመነና እየሰገደ ሶስት ጊዜ ከስላሴ ዙፋን ተንበረከከ፡፡ይሁን ይደረግ የሚል ቃል ከሰማይ ሰማ በወዳጄ በሀብተማርያም አጥንት ቦታህ የምትድን ስለሆነች ፈቃዴ ነው ብሎ ጌታ ቃል ኪዳን ሰጠው፡፡
ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያም በፀሎት ላይ ሳለ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ትዕዛዝ የቆምክባትን ቦታ ምስራቁን፣ ምዕራቡን፣ ሰሜኑን፣ ደቡቡን ባርክ አለው፡፡ ሲባርክም ሶስት አጋንንት በፀሎቱ ስልጣን ታስረው በፊቱ ታዩት፡፡ እነዚህም አጋንንት ከኖህ ጀምሮ ሰውን በማሳት ከኖርን በኋላ ከአንተ ጋር ምን ፀብ አለን አሉ አባታችንም አቡነ ሀብተማርያም በትዕምርተ መስቀል ሲያማትብ ሁለቱን አጋንንት ምድር ተከፍታ ዋጠቻቸው አንዱ ጊዜዬ ስላልደረሰ አታጥፋኝ አለው፡፡ ያን ጊዜ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አቡነ ሀብተማርያምን ይህንን ተወው ጊዜው አልደረሰም አለው፡፡ የጌታ ቃል እንዲህ ብሎ በተናገረ ጊዜ ሰይጣን ከአባታችን ተለይቶ ጠፋ፡፡ ማር 9፡23
ከዚህም በኋላ ዕለተ ሞቱ በደረሰ ጊዜ ለሞቱ ምክንያት የሚሆን ቸነፈር ያዘው፡፡ ጌታችንም በምስጋና ወደ እርሱ መጥቶ ወዳጄ ሀብተማርያም ሆይ ዛሬ ወደአንተ የመጣሁት ከድካም ወደ እረፍት እወስድህ ዘንድ ነው ሰባት የጽድቅ አክሊሎችን አዘጋጅልሃለሁ፡፡
1. ስለ ንፁህ ድንግልናህ፣
2. አለምንና በውስጡ ያለውን ንቀህ በመኖርህ፣
3. ስለ ፍፁም ምንኩስናህ፣
4. ዘወትር አራቱን ወንጌላትን በማንበብህና በመፀለይህ፣
5. ስለ እኔ ብለህ ስለተራብከው፣
6. በጾም ስለተጋደልክ፣
7. ቂምና ጥላቻን፣ ትዕቢትን፣ ትምክህትን፣ በልብህ ውስጥ ባለማስቀመጥህ ስለ ንፁህ ተልዕኮ ክህነትህ፣ ስለ ንፁህ መስዋዕትህ ነው ብሎ ቃል ኪዳን ሰጠው፡፡
በተጨማሪም እኔ የሰጠሁህን ቃል ኪዳን ተስፋ አድርጎ መጽሐፈ ገድልህን ለሚጽፈው ስሙን በመንግስተ ሰማያት በእውነት መጽሐፍ እጽፈዋለሁ፣ ለቤተክርስቲያንህ ዘይትን፣ ወይንን፣ ዕጣንን፣ ህብስትን እስከ ቀዝቃዛ ውሃ ድረስ በአንተ ስም መብዓ የሰጠውን የወደደውን ሁሉ አደርግለታለሁ፡፡ በመንግስተ ሰማያትም ከወዳጆቼ ከቅዱሳን ጋር በደስታ አኖረዋለሁ፡፡ የአቡነ ሀብተማርያም ፈጣሪ ኃጢአቴን ይቅር በለኝ ብሎ ያንተን ስም ጠርቶ ቢለምነኝ ኃጢአቱን አስተሰርይለታለሁ ብሎ ቃልኪዳን ገባለት ይህንንም ካለው በኋላ ጌታችን አፉን ሶስት ጊዜ ሳመው፡፡ ያን ጊዜም ከመድኃኒዓለም ጣዕም ፍቅር የተነሳ ነፍሱ ከስጋው ተለየች መዝ 115/116 ፡ 6 በሰማያዊ መልአክት በምድራውያን ስውራን ቅዱሳን ዘንድ ታላቅ ደስታ ሆነ ህዳር 26 ቀን አረፈ፡፡ ካህናት በመልካም ልብስ ገንዘው በዝማሬ በማህሌት ከቅዱስ አባታችን ከአቡነ ተክለሃይማኖት አጽም ጋር በፃዲቁ መቃብር ቀበሩት፡፡
🤲ኦ አምላከ አቡነ ሀብተ ማርያም ዕቀቦ ወአድኅኖ ወባልሆ እመከራ ሥጋ ወነፍስ ወእምኩሉ ተቃራኒ ወእምኩልነ ክቡር ሀብተ ማርያም ለዓለም ዓለም አሜን ለይኩን ለይኩን::
https://t.me/AbuneHabtemariyamtsdik
Telegram
ጻድቁ አቡነ ሀብተ ማርያም
ስለ #ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ #ሀብተ ማርያም ታሪክ ፣ ገድል ፣ ተአምራት እና መልክዕ እንዲያገኙ ይቀላቀሉ።
ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን የጻድቁ ቤተሰብ ይሁኑ
👇👇👇👇👇👇👇
@AbuneHabtemariyamtsdik
@AbuneHabtemariyamtsdik
👆👆👆👆👆👆👆
Contact @yordanos_26
ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን የጻድቁ ቤተሰብ ይሁኑ
👇👇👇👇👇👇👇
@AbuneHabtemariyamtsdik
@AbuneHabtemariyamtsdik
👆👆👆👆👆👆👆
Contact @yordanos_26
April 5, 2020
🌿ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን አሰሮ ለሰይጣን አግዐዞ ለአዳም ሰላም እምይዕዜሰ ኮነ ፍሥሐ ወሠላም፤
🥰ክርስቶስ በታላቅ ኃይልና ሥልጣን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ፡፡ ዲያብሎስን አሰረው፤ አዳምን ነጻ አወጣው፡፡ ሰላም! ከዛሬ ጀምሮ ሰላም ኾነ፡፡”
🙇♀️እንኳን ለጌታችን ለመድሃኒታችን ለእየሱስ ክርስቶስ የትንሳዔ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤
መልካም በዓል ይሁንልን!!
🥰ክርስቶስ በታላቅ ኃይልና ሥልጣን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ፡፡ ዲያብሎስን አሰረው፤ አዳምን ነጻ አወጣው፡፡ ሰላም! ከዛሬ ጀምሮ ሰላም ኾነ፡፡”
🙇♀️እንኳን ለጌታችን ለመድሃኒታችን ለእየሱስ ክርስቶስ የትንሳዔ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤
መልካም በዓል ይሁንልን!!
April 18, 2020
April 20, 2020
🌿†† † እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም መታሰቢያ በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደሰችሁ†
🛐† “እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል። ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል፥ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል።ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ፥ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋው አይጠፋበትም።" † † ማቴ 10:40
🕊† ሰላም ለፅንሰትከ እማህፀነ ቅድስት ዮስቴና
በብሥራተ ጻድቅ ባሕታዊ ሠናየ ዜና
ሐብተ ማርያም ጴጥሮስ ሐዋርያ ወልደ ዮና
መሐረኒ ምግባረ ጽድቅ ወጸግወኒ ልቦና
አፍቅሮ ቢጽ እኃሥሥ ዘምስለ ፍጽምት
ትህትና::
🕊† ሰላም ለዝክረ ስምከ ዘይትፈቀር እም ወይን
ወዘ ያረስዕ ጽምዓ በድኃራዊ ዘመን
ሃብተ ማርያም ፍቁሩ ለወልደ ማርያም ሕፃን
ከመ ሰአለከ አስተሐሚሞ ተክለሃይማኖት ምዕመን
እስእለከ ተኅድነኒ እምኩሉ ኅዘን
(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)
ረድኤት በረከቱ አይለየን ::
👇👇👇👇👇👇👇
@AbuneHabtemariyamtsdi
😇ብዙ ልጆች አሉት ለስሙ ምስክር
በዙሪያው ያሉትን አብቅቶል ለክብር
ስለ ፍፁም ምልጃው ለኔ ግን ይለያል
ፃድቁ አባቴ ስለው ደስ ይለኛል😇
🛐† “እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል። ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል፥ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል።ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ፥ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋው አይጠፋበትም።" † † ማቴ 10:40
🕊† ሰላም ለፅንሰትከ እማህፀነ ቅድስት ዮስቴና
በብሥራተ ጻድቅ ባሕታዊ ሠናየ ዜና
ሐብተ ማርያም ጴጥሮስ ሐዋርያ ወልደ ዮና
መሐረኒ ምግባረ ጽድቅ ወጸግወኒ ልቦና
አፍቅሮ ቢጽ እኃሥሥ ዘምስለ ፍጽምት
ትህትና::
🕊† ሰላም ለዝክረ ስምከ ዘይትፈቀር እም ወይን
ወዘ ያረስዕ ጽምዓ በድኃራዊ ዘመን
ሃብተ ማርያም ፍቁሩ ለወልደ ማርያም ሕፃን
ከመ ሰአለከ አስተሐሚሞ ተክለሃይማኖት ምዕመን
እስእለከ ተኅድነኒ እምኩሉ ኅዘን
(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)
ረድኤት በረከቱ አይለየን ::
👇👇👇👇👇👇👇
@AbuneHabtemariyamtsdi
😇ብዙ ልጆች አሉት ለስሙ ምስክር
በዙሪያው ያሉትን አብቅቶል ለክብር
ስለ ፍፁም ምልጃው ለኔ ግን ይለያል
ፃድቁ አባቴ ስለው ደስ ይለኛል😇
May 3, 2020
የ እግዚአብሔር ሰላም ለ ሁላችን ይሁን
🔔የፊታችን ግንቦት 26(ታላቁ ጻድቅ አቡነ ሀብተማርያም የተወለዱበት አመታዊ ክብረ በዓል ነው የምንችል በቦታው ተገኝተን የበረከት ተሳታፊ ብንሆን
#በ አዲስ አበባ ሀ/ስብከት የቃሉ በተራራ ደ/መድኃኒት አቡነ ሀብተማርያም: ቅ/ልደታ እና ቅ/አርሴማ ገዳም
❤️ለማያውቁት እያሳወቅን በ ቅዱሱ ቦታ # ግንቦት 26
🤲እጅግ ነፍሰን የሚያስደስት ቦታ
🔔የፊታችን ግንቦት 26(ታላቁ ጻድቅ አቡነ ሀብተማርያም የተወለዱበት አመታዊ ክብረ በዓል ነው የምንችል በቦታው ተገኝተን የበረከት ተሳታፊ ብንሆን
#በ አዲስ አበባ ሀ/ስብከት የቃሉ በተራራ ደ/መድኃኒት አቡነ ሀብተማርያም: ቅ/ልደታ እና ቅ/አርሴማ ገዳም
❤️ለማያውቁት እያሳወቅን በ ቅዱሱ ቦታ # ግንቦት 26
🤲እጅግ ነፍሰን የሚያስደስት ቦታ
May 15, 2020
🌼እንኳን ለዋዜማው አደረሳችሁ 🕊
የምንችል የንግሱ ተካፋይ እንሁን
#ቦታ :- በ አዲስ አበባ ሀ/ስብከት የቃሉ በተራራ ደ/መድኃኒት አቡነ ሀብተማርያም: ቅ/ልደታ እና ቅ/አርሴማ ገዳም
የምንችል የንግሱ ተካፋይ እንሁን
#ቦታ :- በ አዲስ አበባ ሀ/ስብከት የቃሉ በተራራ ደ/መድኃኒት አቡነ ሀብተማርያም: ቅ/ልደታ እና ቅ/አርሴማ ገዳም
June 2, 2020
🕊†† † እንኳን ለታላቁ ጸድቅ ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም የልደት (#ግንቦት 26 )በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደሰችሁ† † †
🌼የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን ::
🌼ሰላም ለልደትከ እማህፀነ ቅድስት ዮስቴና
በብሥራተ ጻድቅ ባሕታዊ ሠናየ ዜና
ሐብተ ማርያም ጴጥሮስ ሐዋርያ ወልደ ዮና
መሐረኒ ምግባረ ጽድቅ ወጸግወኒ ልቦና
አፍቅሮ ቢጽ እኃሥሥ ዘምስለ ፍጽምት ትሕትና::
🌼ሰላም ለአራኅከ ነሣኤ ኅለት ዘአሚን::
ዘይትባሕዩ ቦቱ አባግዒከ ዝርዋን::
ሀብተ ማርያም መርስ ሀብተ ማርያም ዛኅን::
ይሱቀኒ እምትንታኔ ጸሎትከ በትረ ሐፂን::
ለቁረተ ነፍስየ ካዕበ ቃልከ ክዳን::
🙇♀️በአለም የተበተኑ በጏች የተባሉ ልጆችህ የሚጠበቅበት የእምነት ዘንግን ለጨበጠ መሐል እጅህ ሰላምታ ይገባል::ጻድቁ አባቴ ሀብተማርያም ሆይ የዚች አለም ጸጥታዋና ሰላሟ አንተ ነህ እኮ እኔን ለመውደቅ የተፍገመገምኩትን እንደብረት ዘንግ የሆነ ጸሎትህ ከወደቅኩበት መሬት ያንሳኝ ይደግፈኝ ሁለተኛም የጏሰቆለች ነፍሴን ቃልኪዳንህ አይለያት::(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)
🛐ኦ አምላከ አቡነ ሀብተ ማርያም ዕቀቦ ወአድኅኖ ወባልሆ እመከራ ሥጋ ወነፍስ ወእምኩሉ ተቃራኒ ወእምኩልነ ክቡር ሀብተ ማርያም ለዓለም ዓለም አሜን ለይኩን ለይኩን::
https://www.youtube.com/watch?v=_5APlmAq2MY&feature=share
🌼የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን ::
🌼ሰላም ለልደትከ እማህፀነ ቅድስት ዮስቴና
በብሥራተ ጻድቅ ባሕታዊ ሠናየ ዜና
ሐብተ ማርያም ጴጥሮስ ሐዋርያ ወልደ ዮና
መሐረኒ ምግባረ ጽድቅ ወጸግወኒ ልቦና
አፍቅሮ ቢጽ እኃሥሥ ዘምስለ ፍጽምት ትሕትና::
🌼ሰላም ለአራኅከ ነሣኤ ኅለት ዘአሚን::
ዘይትባሕዩ ቦቱ አባግዒከ ዝርዋን::
ሀብተ ማርያም መርስ ሀብተ ማርያም ዛኅን::
ይሱቀኒ እምትንታኔ ጸሎትከ በትረ ሐፂን::
ለቁረተ ነፍስየ ካዕበ ቃልከ ክዳን::
🙇♀️በአለም የተበተኑ በጏች የተባሉ ልጆችህ የሚጠበቅበት የእምነት ዘንግን ለጨበጠ መሐል እጅህ ሰላምታ ይገባል::ጻድቁ አባቴ ሀብተማርያም ሆይ የዚች አለም ጸጥታዋና ሰላሟ አንተ ነህ እኮ እኔን ለመውደቅ የተፍገመገምኩትን እንደብረት ዘንግ የሆነ ጸሎትህ ከወደቅኩበት መሬት ያንሳኝ ይደግፈኝ ሁለተኛም የጏሰቆለች ነፍሴን ቃልኪዳንህ አይለያት::(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)
🛐ኦ አምላከ አቡነ ሀብተ ማርያም ዕቀቦ ወአድኅኖ ወባልሆ እመከራ ሥጋ ወነፍስ ወእምኩሉ ተቃራኒ ወእምኩልነ ክቡር ሀብተ ማርያም ለዓለም ዓለም አሜን ለይኩን ለይኩን::
https://www.youtube.com/watch?v=_5APlmAq2MY&feature=share
YouTube
መልክአ አቡነ ሃብተ ማርያም ለመማሪያ ይሆን ዘንድ የተዘጋጀ በሊቀ ካህናት ነቅዓ ጥበብ የማነ ብርሃን
#ዝማሬ
🛐ጽሩይእምወርቅ
ጽሩይ እምወርቅ ወእምብሩር ንጡፍ ወኅሩይ እምአእላፍ
ሐብተ ማርያም መልአክ ዘውገ ኪሩብ ቀሊለ ክንፍ
አማን ስሙዐ ዜና እስከ አጽናፍ፡፡
https://www.youtube.com/watch?v=Lf1Dtjnx8Pk&feature=share
🛐ጽሩይእምወርቅ
ሐብተ ማርያም መልአክ ዘውገ ኪሩብ ቀሊለ ክንፍ
አማን ስሙዐ ዜና እስከ አጽናፍ፡፡
https://www.youtube.com/watch?v=Lf1Dtjnx8Pk&feature=share
YouTube
የጻድቁ አቡነ ሃብተማርያም ጸሎታቸው እና ልመናቸው አይለየን!
#ዝማሬ
ጻድቁ ሀብተማርያም
መጥተናል እኛ ልጆችህ
አድነን አውጣን ከፈተና
አልብሰን የብርሃንን ፋና
ፃድቁ - - - ሰባት አክሊላትን
ፃድቁ - - - በራሱ የደፋ ፃድቁ
ፃድቁ - - - በጾም በፀሎት ነው
ፃድቁ - - - ሰይጣንን ያጠፋ
ፃድቁ - - - ፅድቅን የታጠቀው
ፃድቁ - - - የእግዚአብሔር አገልጋይ
ፃድቁ - - - ፃድቁ አባታችን
ፃድቁ - - - የኢትዮጵያ ሲሳይ
ፃድቁ - - - የዮስቴና ጸጋ
ፃድቁ - - - የፍሬ ብሩክ
ፃድቁ - - - ለኛ ለልጆችህ
ፃድቁ - - - መመኪያ የሆንክ
ፃድቁ - - - በምልጃህ አድለን
ፃድቁ - - - ፍቅርና ሰላም
ፃድቁ - - - ፃድቁ አባታችን
ፃድቁ - - - ሀብተ ማርያም
ፃድቁ - - - ከሱራፌል ጋራ
ፃድቁ - - - ለማቅረብ ምስጋና
ፃድቁ - - - ፅድቅን ተጎናጽፎ
ፃድቁ - - - ሀብተ ንፅሕና
ፃድቁ - - - በደብረ ሊባኖስ
ፃድቁ - - - ይሰበይ ላይ ያለው
ፃድቁ - - - ፃድቁ አባታችን
ፃድቁ - - - ሀብተማርያም ነው
ፃድቁ - - - ባለመቶ ፍሬ
ፃድቁ - - - ሀብተማርያም
ፃድቁ - - - ቤታችንን ሞላው
ፃድቁ - - - ፍቅርና ሰላም
ፃድቁ - - - ሚስጥርን ተካፈልክ
ፃድቁ - - - ከጽርሐአርያም
ፃድቁ - - - ፃድቁ አባታችን
ፃድቁ - - - ሀብተማርያም
ጻድቁ ሀብተማርያም
መጥተናል እኛ ልጆችህ
አድነን አውጣን ከፈተና
አልብሰን የብርሃንን ፋና
ፃድቁ - - - ሰባት አክሊላትን
ፃድቁ - - - በራሱ የደፋ ፃድቁ
ፃድቁ - - - በጾም በፀሎት ነው
ፃድቁ - - - ሰይጣንን ያጠፋ
ፃድቁ - - - ፅድቅን የታጠቀው
ፃድቁ - - - የእግዚአብሔር አገልጋይ
ፃድቁ - - - ፃድቁ አባታችን
ፃድቁ - - - የኢትዮጵያ ሲሳይ
ፃድቁ - - - የዮስቴና ጸጋ
ፃድቁ - - - የፍሬ ብሩክ
ፃድቁ - - - ለኛ ለልጆችህ
ፃድቁ - - - መመኪያ የሆንክ
ፃድቁ - - - በምልጃህ አድለን
ፃድቁ - - - ፍቅርና ሰላም
ፃድቁ - - - ፃድቁ አባታችን
ፃድቁ - - - ሀብተ ማርያም
ፃድቁ - - - ከሱራፌል ጋራ
ፃድቁ - - - ለማቅረብ ምስጋና
ፃድቁ - - - ፅድቅን ተጎናጽፎ
ፃድቁ - - - ሀብተ ንፅሕና
ፃድቁ - - - በደብረ ሊባኖስ
ፃድቁ - - - ይሰበይ ላይ ያለው
ፃድቁ - - - ፃድቁ አባታችን
ፃድቁ - - - ሀብተማርያም ነው
ፃድቁ - - - ባለመቶ ፍሬ
ፃድቁ - - - ሀብተማርያም
ፃድቁ - - - ቤታችንን ሞላው
ፃድቁ - - - ፍቅርና ሰላም
ፃድቁ - - - ሚስጥርን ተካፈልክ
ፃድቁ - - - ከጽርሐአርያም
ፃድቁ - - - ፃድቁ አባታችን
ፃድቁ - - - ሀብተማርያም
June 3, 2020
🕊እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደረሳችሁ አሜን:፡
† እግዚአብሔር የቅዱሳንን ነፍስ ይጠብቃል ከሃጢአት እጅም ያድናቸዋል::† መዝ.96፡10
የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን ::
† በአለም የተበተኑ በጏች የተባሉ ልጆችህ የሚጠበቅበት የእምነት ዘንግን ለጨበጠ መሐል እጅህ ሰላምታ ይገባል::
ጻድቁ አባቴ ሀብተማርያም ሆይ የዚች አለም ጸጥታዋና ሰላሟ አንተ ነህ እኮ እኔን ለመውደቅ የተፍገመገምኩትን እንደብረት ዘንግ የሆነ ጸሎትህ ከወደቅኩበት መሬት ያንሳኝ ይደግፈኝ ሁለተኛም የጏሰቆለች ነፍሴን ቃልኪዳንህ አይለያት::
🌸ሰላም ለልብከ ለቃለ መጻህፍት ምዕራፍ ::ዘበውስቴታ ይትረከብ መራኁተ ጽድቅ ዘእደ ኬፋ::ሀብተ ማርያም መልአክ ዓቃቤ ትእዛዙ ለአልፋ ይሡቀኒ እምትንታኔ አልብየ ተስፋ::ጸውዖ ስምከ ዘአልቦ ዘለፋ::
🤲ኦ አምላከ አቡነ ሀብተ ማርያም ዕቀቦ ወአድኅኖ ወባልሆ እመከራ ሥጋ ወነፍስ ወእምኩሉ ተቃራኒ ወእምኩልነ ክቡር ሀብተ ማርያም ለዓለም ዓለም አሜን ለይኩን ለይኩን::
(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)
† እግዚአብሔር የቅዱሳንን ነፍስ ይጠብቃል ከሃጢአት እጅም ያድናቸዋል::† መዝ.96፡10
የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን ::
† በአለም የተበተኑ በጏች የተባሉ ልጆችህ የሚጠበቅበት የእምነት ዘንግን ለጨበጠ መሐል እጅህ ሰላምታ ይገባል::
ጻድቁ አባቴ ሀብተማርያም ሆይ የዚች አለም ጸጥታዋና ሰላሟ አንተ ነህ እኮ እኔን ለመውደቅ የተፍገመገምኩትን እንደብረት ዘንግ የሆነ ጸሎትህ ከወደቅኩበት መሬት ያንሳኝ ይደግፈኝ ሁለተኛም የጏሰቆለች ነፍሴን ቃልኪዳንህ አይለያት::
🌸ሰላም ለልብከ ለቃለ መጻህፍት ምዕራፍ ::ዘበውስቴታ ይትረከብ መራኁተ ጽድቅ ዘእደ ኬፋ::ሀብተ ማርያም መልአክ ዓቃቤ ትእዛዙ ለአልፋ ይሡቀኒ እምትንታኔ አልብየ ተስፋ::ጸውዖ ስምከ ዘአልቦ ዘለፋ::
🤲ኦ አምላከ አቡነ ሀብተ ማርያም ዕቀቦ ወአድኅኖ ወባልሆ እመከራ ሥጋ ወነፍስ ወእምኩሉ ተቃራኒ ወእምኩልነ ክቡር ሀብተ ማርያም ለዓለም ዓለም አሜን ለይኩን ለይኩን::
(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)
July 3, 2020
† እግዚአብሔር የቅዱሳንን ነፍስ ይጠብቃል ከሃጢአት እጅም ያድናቸዋል::† መዝ.96፡10
🕊እንኳን ለታላቁ ጸድቅ ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደረሳችሁ አሜን፡፡
🕊ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያም በፈሪሃ እግዚአብሔር በትምህርት አደገ፡፡ ከዕለታት በአንድ ቀን ካህናቱ በቤተክርስቲያን ምህላ ሲያደርሱ "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" እያሉ ሲፀልዩ ሰምቶ በልቡናው ይህች ፀሎት በጣም ጥሩና መልካም ፀሎት ናት አለ በዚህ ፀሎት ከዓለም አሳችነት ከገሃነም እሳት እንድንባት ዘንድ አውቃለሁ የንስሐ መንገድ ናት ብሎ ተናገረ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም በዚህች ፀሎት ተጠምዶ በጾምና በፀሎት በስደት የሚኖር ሆነ::
🙇♀️ሰላም ለዝክረ ስምከ ዘይትፈቀር እም ወይን
ወዘ ያረስዕ ጽምዓ በድኃራዊ ዘመን
ሐብተ ማርያም ፍቁሩ ለወልደ ማርያም ሕፃን
ከመ ሰአለከ አስተሐሚሞ ተልከሃይማኖት ምዕመን
እስእለከ ተኅድነኒ እምኩሉ ኅዘን:🤲🤲🤲
(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)❤️
🕊ትክበር ነፍስየ በቅድሜከ ዮም
ባርከኒ አባ(5) ሀብተማርያም
🕊እንኳን ለታላቁ ጸድቅ ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደረሳችሁ አሜን፡፡
🕊ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያም በፈሪሃ እግዚአብሔር በትምህርት አደገ፡፡ ከዕለታት በአንድ ቀን ካህናቱ በቤተክርስቲያን ምህላ ሲያደርሱ "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" እያሉ ሲፀልዩ ሰምቶ በልቡናው ይህች ፀሎት በጣም ጥሩና መልካም ፀሎት ናት አለ በዚህ ፀሎት ከዓለም አሳችነት ከገሃነም እሳት እንድንባት ዘንድ አውቃለሁ የንስሐ መንገድ ናት ብሎ ተናገረ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም በዚህች ፀሎት ተጠምዶ በጾምና በፀሎት በስደት የሚኖር ሆነ::
🙇♀️ሰላም ለዝክረ ስምከ ዘይትፈቀር እም ወይን
ወዘ ያረስዕ ጽምዓ በድኃራዊ ዘመን
ሐብተ ማርያም ፍቁሩ ለወልደ ማርያም ሕፃን
ከመ ሰአለከ አስተሐሚሞ ተልከሃይማኖት ምዕመን
እስእለከ ተኅድነኒ እምኩሉ ኅዘን:🤲🤲🤲
(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)❤️
🕊ትክበር ነፍስየ በቅድሜከ ዮም
ባርከኒ አባ(5) ሀብተማርያም
August 1, 2020
#ነሐሴ 26 ፅንሰቱ ለ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም
†† † እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደሰችሁ† † †
† † † ሰላም ለፅንሰትከ እማህፀነ ቅድስት ዮስቴና
በብሥራተ ጻድቅ ባሕታዊ ሠናየ ዜና
ሐብተ ማርያም ጴጥሮስ ሐዋርያ ወልደ ዮና
መሐረኒ ምግባረ ጽድቅ ወጸግወኒ ልቦና
አፍቅሮ ቢጽ እኃሥሥ ዘምስለ ፍጽምት ትሕትና::
(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)
#አቡነ_ሃብተማርያም
አባታችን ታላቁ ጻድቅ አባታችን #አቡነ_ሃብተማርያም የተወለዱት በመንዝ አውራጃ ልዩ ስሙ የራዊ በተባለ ቦታ ሲሆን የአባታቸው ስም ፍሬ ብሩክ የእናታቸው ስም ዮስቴና ይባላል፡፡ ሁለቱም በሕግ ጋብቻ ጸንተው ሕገ እግዚአብሔርን ጠብቀው ምግባር ቱሩፋት ሰርተው በንጽህና በቅድስና ይኖሩ ነበር፡፡ ሆኖም ልጅ አለነበራቸውም፡፡ በዚህ ሁኔታ ያዘኑ ቅድስት ዮስቴና ማለት እናታቸው መንነው በአከባቢያቸው ከሚገኝ ጫካ ውስጥ ዋሻ ፈልገው ገብተው ዘጉ፡፡ በዚያም አንድ መናኝ መነኩሴ አግኝተዋቸው እግዚአብሔር በቅድስቲቱ ያለው ድብቅ ነገር ስለገለጠላቸው አንቺ ለምንኩስና የተፈቀደልሽ አይደለሽም ወደ ቤትሽ ግቢ ጸሎቱ ለዓለም ሁሉ የሚጠቅም ሰው ሁሉ የሚማጸነው ስሙ፣ ገድሉ ትሩፋቱ በዓለም ሁሉ የሚነገርለት ወንድ ልጅ ትወልጃለሽ አሏቸው፡፡ የእግዚአብሔርን ድንቅ ተዓምር የሰሙ ቅድስት ዮስቴናም እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ወደ ቤቸው ተመለሱ፡፡
የተናገረውን የማያስቀር አምላክ በቸርነቱ ጎበኛቸውና ነሐሴ 26 ቀን ጸነሱ፡፡ ግንቦት 26 ቀንም ደም ግባታቸው እንደ ንጋት ኮከብ ያማሩ ሃብተማርያም ተወለዱ፡፡ እግዚአብሔር ለቅድስና ሥራ ስለመረጣቸው በእናተቸው ጀርባ ታዝለው ወደ ቤተክርስቲያን ሄደው በሕጻን አንደበታቸው ከቀዳሹ ካህን ጋር “እግዚኦ ማሐረነ ክርስቶስ” በማለት ይጸልዩ ነበር፡፡ ባደጉም ጊዜ ይህን ጸሎት ደጋግመው ይጸልዩ ነበር፡፡ ላባቸውም እስኪንጠባጠብ ድረስ በመስገድ ይጋደሉ ነበር፡፡ አንድ ቀንም ከአባታቸው ጎን እንደ ተኙ በድንገት እግዚአብሔር በድምጽ “ሀብተማርያም ሆይ! አንተን የተመረጠ ዕቃ አድርጌሃለሁና ቃሌን ለተመረጡ ሰዎች ተናገር” አላቸው፡፡ ይህን ግን የተበሰረላቸው የቤተሰቦቻቸውን ከብቶች በሚጠብቁበት ጊዜ ነበር፡፡ እድሜያቸው እየገፋ ሲሄድ አባታቸው ትምህርት ቤት አስገቡአቸው፡፡ ለአቅመ አዳም በደረሱ ጊዜ ሚስት አጩላቸው፤ እርሳቸው ግን የድንግልናን ህይወት በመምረጥ ከወላጃቸው ቤት ኮብልለው ገዳም ገቡ፡፡
“ልጄ ሆይ እራስህን ለእግዚአብሔር ታስገዛ ዘንድ ወደ ገዳም ብትሄድ ሰውነትህ ለመከራ አዘጋጅ፡፡” መጽሐፈ ሲራክ 2፡1.
በዚያን አባ ሳሙኤል ለሚባሉ በረዳትነት ሲያገለግሉብዙ ገቢረ ተዓምራት ተደርጎላቸዋል፡፡ ዛሬ ይሰበይ ገዳም ተብሎ በሚጠራው ሥፍራ ለሦስት ወራት ጽሙድ እንደበሬ ትጉህ እንደ ገበሬ እንዲሉ በጾም በጸሎት ተጠምደው ሳለ መታሰቢያህን በዚህ ዋሻ አደርግልሃለሁ በማለት እግዚአብሔር ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡ ጊዜ እረፍታቸው በደረሰ ጊዜ ጌታ ተገልጦላቸው ስለ ተጋድሎአቸውና ስለንጽህናቸው ሳባት አክሊል እንደሚቀበሉ ነግሯቸዋል፡፡
በ490 ዓ.ም ህዳር 26 ቀን ዐርፈው በደብረሊባኖስ ገዳም መካነ ቅዱሳን ቀበሯቸው፡፡
የአባታችን የጻድቁ አቡነ ሀብተማርያም ረድኤት፣ በረከት፣ ምልጃና ቃል ኪዳናቸው አይለየን፡፡
✞✞✞✞✞
#አቡነ #ተክለሃይማኖት አና #አቡነ #ሃብተማርያም
✞
#ያን ጊዜ ክቡር የሆነ #አቡነ_ተክለሃይማኖት ጠርቶኝ ልጄ #ሀብተ_ማርያም ሆይ ፈጣሪየ እግዚአብሔር ስለ ወደደህ ብዙ ምህርኮ እንደአገኝህ በአንተ ፈጽሞ ደስ ይለኛል አለኝ ፤
#ነገር ግን የሞለምንክ አንድ ነገር አለና እሽ በለኝ ቢለኝ አቤቱ ጌታዩ ምንድን ነው ነገሩ አልሁት ፣
#ክቡር አባታችን አባ ተክለሃይማኖትም ከተቀበርኩበት ቦታ እንድትቀብር ቃል ኪዳን ግባልኝ አለኝ፤
ይንን አደርግ ዘንድ ስለምን ትለምነኛለህ ብየ ብመልስለት፣ እነሆ በሀገሬ ላይ የታዘዙ አምስ መቅሰፍቶች አሉና ስለዚህ ነው ፤ እሊሁም አንዱ መብረቅ ነው ፣ ሁለተኛው ቸነፈር ነው ፤ ሦስተኛው የረኃብ ጦር ነው ፣ አራተኛ ወረርሽኝ ነው ፡፡ አምስተኛ የእሳት ቃጠሎ ነው ፤ የአንተ አጽም በውስጡ የተቀበረ እንደ ሆነ አጥንቴ የተቀበረባት ሀገር ከእንዚህ መቅስፍታት ትድናለች፣
#……ልጄ ሀብተማርያም ሆይ አንተ የማታውቀው ከፈጣሪያችን ከእግዚአብሄር የተሰጠህ እኔ የማውቀው ክብር አለህና ስለዚህ ነው አለኝ ፣ ይልቁንስ እንዳልኩክ በተቀበርኩበት ቦታ እንተቀበርልኝ ቃል ኪዳን ግባልኝ ብሎ መላልሶ ማለደኝ.
✞ #ከገድላቸው
#አቡነ_ሀብተ_ማርያም በቃል ኪዳናቸው ሀገራችንን ከአምስቱ መቅሰፍታት ይጠብቁልን አሜን !
በአ.አ በዓሉ በድምቀት ከሚከበርባቸው አድባራት አንዱ በቃሌ ተራራ ደብር መድኃኒት አቡነ ሃብተማርያም ገዳም አንዱ ነው ::
አቅጣጫ አስኮ አካባቢ
#ፅንሰታቸው ነሐሴ 26
#ልደታቸው ግንቦት 26
#ዕረፍታቸው ህዳር 26
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
†† † እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደሰችሁ† † †
† † † ሰላም ለፅንሰትከ እማህፀነ ቅድስት ዮስቴና
በብሥራተ ጻድቅ ባሕታዊ ሠናየ ዜና
ሐብተ ማርያም ጴጥሮስ ሐዋርያ ወልደ ዮና
መሐረኒ ምግባረ ጽድቅ ወጸግወኒ ልቦና
አፍቅሮ ቢጽ እኃሥሥ ዘምስለ ፍጽምት ትሕትና::
(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)
#አቡነ_ሃብተማርያም
አባታችን ታላቁ ጻድቅ አባታችን #አቡነ_ሃብተማርያም የተወለዱት በመንዝ አውራጃ ልዩ ስሙ የራዊ በተባለ ቦታ ሲሆን የአባታቸው ስም ፍሬ ብሩክ የእናታቸው ስም ዮስቴና ይባላል፡፡ ሁለቱም በሕግ ጋብቻ ጸንተው ሕገ እግዚአብሔርን ጠብቀው ምግባር ቱሩፋት ሰርተው በንጽህና በቅድስና ይኖሩ ነበር፡፡ ሆኖም ልጅ አለነበራቸውም፡፡ በዚህ ሁኔታ ያዘኑ ቅድስት ዮስቴና ማለት እናታቸው መንነው በአከባቢያቸው ከሚገኝ ጫካ ውስጥ ዋሻ ፈልገው ገብተው ዘጉ፡፡ በዚያም አንድ መናኝ መነኩሴ አግኝተዋቸው እግዚአብሔር በቅድስቲቱ ያለው ድብቅ ነገር ስለገለጠላቸው አንቺ ለምንኩስና የተፈቀደልሽ አይደለሽም ወደ ቤትሽ ግቢ ጸሎቱ ለዓለም ሁሉ የሚጠቅም ሰው ሁሉ የሚማጸነው ስሙ፣ ገድሉ ትሩፋቱ በዓለም ሁሉ የሚነገርለት ወንድ ልጅ ትወልጃለሽ አሏቸው፡፡ የእግዚአብሔርን ድንቅ ተዓምር የሰሙ ቅድስት ዮስቴናም እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ወደ ቤቸው ተመለሱ፡፡
የተናገረውን የማያስቀር አምላክ በቸርነቱ ጎበኛቸውና ነሐሴ 26 ቀን ጸነሱ፡፡ ግንቦት 26 ቀንም ደም ግባታቸው እንደ ንጋት ኮከብ ያማሩ ሃብተማርያም ተወለዱ፡፡ እግዚአብሔር ለቅድስና ሥራ ስለመረጣቸው በእናተቸው ጀርባ ታዝለው ወደ ቤተክርስቲያን ሄደው በሕጻን አንደበታቸው ከቀዳሹ ካህን ጋር “እግዚኦ ማሐረነ ክርስቶስ” በማለት ይጸልዩ ነበር፡፡ ባደጉም ጊዜ ይህን ጸሎት ደጋግመው ይጸልዩ ነበር፡፡ ላባቸውም እስኪንጠባጠብ ድረስ በመስገድ ይጋደሉ ነበር፡፡ አንድ ቀንም ከአባታቸው ጎን እንደ ተኙ በድንገት እግዚአብሔር በድምጽ “ሀብተማርያም ሆይ! አንተን የተመረጠ ዕቃ አድርጌሃለሁና ቃሌን ለተመረጡ ሰዎች ተናገር” አላቸው፡፡ ይህን ግን የተበሰረላቸው የቤተሰቦቻቸውን ከብቶች በሚጠብቁበት ጊዜ ነበር፡፡ እድሜያቸው እየገፋ ሲሄድ አባታቸው ትምህርት ቤት አስገቡአቸው፡፡ ለአቅመ አዳም በደረሱ ጊዜ ሚስት አጩላቸው፤ እርሳቸው ግን የድንግልናን ህይወት በመምረጥ ከወላጃቸው ቤት ኮብልለው ገዳም ገቡ፡፡
“ልጄ ሆይ እራስህን ለእግዚአብሔር ታስገዛ ዘንድ ወደ ገዳም ብትሄድ ሰውነትህ ለመከራ አዘጋጅ፡፡” መጽሐፈ ሲራክ 2፡1.
በዚያን አባ ሳሙኤል ለሚባሉ በረዳትነት ሲያገለግሉብዙ ገቢረ ተዓምራት ተደርጎላቸዋል፡፡ ዛሬ ይሰበይ ገዳም ተብሎ በሚጠራው ሥፍራ ለሦስት ወራት ጽሙድ እንደበሬ ትጉህ እንደ ገበሬ እንዲሉ በጾም በጸሎት ተጠምደው ሳለ መታሰቢያህን በዚህ ዋሻ አደርግልሃለሁ በማለት እግዚአብሔር ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡ ጊዜ እረፍታቸው በደረሰ ጊዜ ጌታ ተገልጦላቸው ስለ ተጋድሎአቸውና ስለንጽህናቸው ሳባት አክሊል እንደሚቀበሉ ነግሯቸዋል፡፡
በ490 ዓ.ም ህዳር 26 ቀን ዐርፈው በደብረሊባኖስ ገዳም መካነ ቅዱሳን ቀበሯቸው፡፡
የአባታችን የጻድቁ አቡነ ሀብተማርያም ረድኤት፣ በረከት፣ ምልጃና ቃል ኪዳናቸው አይለየን፡፡
✞✞✞✞✞
#አቡነ #ተክለሃይማኖት አና #አቡነ #ሃብተማርያም
✞
#ያን ጊዜ ክቡር የሆነ #አቡነ_ተክለሃይማኖት ጠርቶኝ ልጄ #ሀብተ_ማርያም ሆይ ፈጣሪየ እግዚአብሔር ስለ ወደደህ ብዙ ምህርኮ እንደአገኝህ በአንተ ፈጽሞ ደስ ይለኛል አለኝ ፤
#ነገር ግን የሞለምንክ አንድ ነገር አለና እሽ በለኝ ቢለኝ አቤቱ ጌታዩ ምንድን ነው ነገሩ አልሁት ፣
#ክቡር አባታችን አባ ተክለሃይማኖትም ከተቀበርኩበት ቦታ እንድትቀብር ቃል ኪዳን ግባልኝ አለኝ፤
ይንን አደርግ ዘንድ ስለምን ትለምነኛለህ ብየ ብመልስለት፣ እነሆ በሀገሬ ላይ የታዘዙ አምስ መቅሰፍቶች አሉና ስለዚህ ነው ፤ እሊሁም አንዱ መብረቅ ነው ፣ ሁለተኛው ቸነፈር ነው ፤ ሦስተኛው የረኃብ ጦር ነው ፣ አራተኛ ወረርሽኝ ነው ፡፡ አምስተኛ የእሳት ቃጠሎ ነው ፤ የአንተ አጽም በውስጡ የተቀበረ እንደ ሆነ አጥንቴ የተቀበረባት ሀገር ከእንዚህ መቅስፍታት ትድናለች፣
#……ልጄ ሀብተማርያም ሆይ አንተ የማታውቀው ከፈጣሪያችን ከእግዚአብሄር የተሰጠህ እኔ የማውቀው ክብር አለህና ስለዚህ ነው አለኝ ፣ ይልቁንስ እንዳልኩክ በተቀበርኩበት ቦታ እንተቀበርልኝ ቃል ኪዳን ግባልኝ ብሎ መላልሶ ማለደኝ.
✞ #ከገድላቸው
#አቡነ_ሀብተ_ማርያም በቃል ኪዳናቸው ሀገራችንን ከአምስቱ መቅሰፍታት ይጠብቁልን አሜን !
በአ.አ በዓሉ በድምቀት ከሚከበርባቸው አድባራት አንዱ በቃሌ ተራራ ደብር መድኃኒት አቡነ ሃብተማርያም ገዳም አንዱ ነው ::
አቅጣጫ አስኮ አካባቢ
#ፅንሰታቸው ነሐሴ 26
#ልደታቸው ግንቦት 26
#ዕረፍታቸው ህዳር 26
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
August 31, 2020
ጻድቁ አቡነ ሀብተ ማርያም pinned «#ነሐሴ 26 ፅንሰቱ ለ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም †† † እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደሰችሁ† † † † † † ሰላም ለፅንሰትከ እማህፀነ ቅድስት ዮስቴና በብሥራተ ጻድቅ ባሕታዊ ሠናየ ዜና ሐብተ ማርያም ጴጥሮስ ሐዋርያ ወልደ ዮና መሐረኒ ምግባረ ጽድቅ ወጸግወኒ ልቦና አፍቅሮ ቢጽ እኃሥሥ ዘምስለ ፍጽምት ትሕትና:: (መልክአ አቡነ…»
September 2, 2020
🌹🌹🌹እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም በዓል እና ዘመነ ጽጌ በሰላም በጤና አደረሰን አደረሳችሁ አሜን፡፡🌹🌹🌹
🌼የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን ::
🌷ሰላም ለጻአተ ነፍሰከ እምቤተ ሥጋሃ ንጽሕ:: እሰከነ ትገብእ ድኅረ በትህዛዘ ክርስቶስ መሢሕ:: ሀብተ ማርያም ርግብ ሀብተ ማርያም የዋህ:: አብሥረኒ ብሥራተ ጽድቅ ከመ ብሥራተ አብ ኖኅ::በኂሩተ አምላክ ባዕል ወአኮ በፍትሕ::
🌸ከአሁን በፊት ከሰማይ በታች ያልተሰማ የሚያስደንቅ ነገር በ ደብረ ሊባኖስ ውስጥ ተሰማ በደልን ሁሉ በአማላጅነቱ የሚያስተሰርይ የአባታችን የአቡነ ሀብተማርያምን ድንቅ ስራን የባህር ውሃ መስክራለችና የጻድቁ አባታችን የአቡነ ሀብተማርያም አምላክ እንዲሁም የሁላችን አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ እኛን ልጆችህን ከመከራ ስጋ ከመከራ ነፍስ ሰውረን ከዳቢሎስ ውጊያም ለዘለዓለሙ ጠብቀን ::
🌺 ጻዲቁ አቡነ ሀብተማርያም በፈሪሃ እግዚአብሔር በትምህርት አደገ፡፡ ከዕለታት በአንድ ቀን ካህናቱ በቤተክርስቲያን ምህላ ሲያደርሱ "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" እያሉ ሲፀልዩ ሰምቶ በልቡናው ይህች ፀሎት በጣም ጥሩና መልካም ፀሎት ናት አለ በዚህ ፀሎት ከዓለም አሳችነት ከገሃነም እሳት እንድንባት ዘንድ አውቃለሁ የንስሐ መንገድ ናት ብሎ ተናገረ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም በዚህች ፀሎት ተጠምዶ በጾምና በፀሎት በስደት የሚኖር ሆነ::
🌻 አምላከ አቡነ ሀብተማርያም ሆይ እኛን ሁላችንን ከተቃጣ መዓት ከታዘዘ መቅሰፍት ከድንገተኛ ሞት ሰውረን ለዘለዓለሙ አሜን::
(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)
🌼የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን ::
🌷ሰላም ለጻአተ ነፍሰከ እምቤተ ሥጋሃ ንጽሕ:: እሰከነ ትገብእ ድኅረ በትህዛዘ ክርስቶስ መሢሕ:: ሀብተ ማርያም ርግብ ሀብተ ማርያም የዋህ:: አብሥረኒ ብሥራተ ጽድቅ ከመ ብሥራተ አብ ኖኅ::በኂሩተ አምላክ ባዕል ወአኮ በፍትሕ::
🌸ከአሁን በፊት ከሰማይ በታች ያልተሰማ የሚያስደንቅ ነገር በ ደብረ ሊባኖስ ውስጥ ተሰማ በደልን ሁሉ በአማላጅነቱ የሚያስተሰርይ የአባታችን የአቡነ ሀብተማርያምን ድንቅ ስራን የባህር ውሃ መስክራለችና የጻድቁ አባታችን የአቡነ ሀብተማርያም አምላክ እንዲሁም የሁላችን አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ እኛን ልጆችህን ከመከራ ስጋ ከመከራ ነፍስ ሰውረን ከዳቢሎስ ውጊያም ለዘለዓለሙ ጠብቀን ::
🌺 ጻዲቁ አቡነ ሀብተማርያም በፈሪሃ እግዚአብሔር በትምህርት አደገ፡፡ ከዕለታት በአንድ ቀን ካህናቱ በቤተክርስቲያን ምህላ ሲያደርሱ "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" እያሉ ሲፀልዩ ሰምቶ በልቡናው ይህች ፀሎት በጣም ጥሩና መልካም ፀሎት ናት አለ በዚህ ፀሎት ከዓለም አሳችነት ከገሃነም እሳት እንድንባት ዘንድ አውቃለሁ የንስሐ መንገድ ናት ብሎ ተናገረ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም በዚህች ፀሎት ተጠምዶ በጾምና በፀሎት በስደት የሚኖር ሆነ::
🌻 አምላከ አቡነ ሀብተማርያም ሆይ እኛን ሁላችንን ከተቃጣ መዓት ከታዘዘ መቅሰፍት ከድንገተኛ ሞት ሰውረን ለዘለዓለሙ አሜን::
(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)
October 7, 2020
November 4, 2020
#አቡነ_ሀብተማርያም_ጥቅምት26
“ዝክረ ጻድቅ ለዓለም ይሄሉ፡፡”መዝ 111/112፡6
እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደረሳችሁ አሜን፡፡
🙇♀️ሰላም ለዝክረ ስምክ፡- በዃለኛው ዘመን የዚህን ዓለም ረሃብና ጥም የሚያስረሳና ከወይን ዘለላ ይልቅ ለሚወደድ ስም አጠራርህ ሰላምታ ይገባል፡፡ ህጻን የሆነ የማርያም ልጅ ወዳጅ ጻድቁ አባቴ አቡነ ሀብተ ማርያም ሆይ በቦታው ታርፍለት ዘንድ ጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት አጥብቆ እንደ ለመነ እኔም አገልጋይ ከሀዘን ሁሉ ታድነኝና በቤቴም ታርፍ ዘንድ እለምነሃለሁ፡፡
🔔የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን ::
🙇♀️አምላከ አቡነ ሀብተማርያም ሆይ እኛን ሁላችንን ከተቃጣ መዓት ከታዘዘ መቅሰፍት ከድንገተኛ ሞት ሰውረን ለዘለዓለሙ አሜን::
“ዝክረ ጻድቅ ለዓለም ይሄሉ፡፡”መዝ 111/112፡6
እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደረሳችሁ አሜን፡፡
🙇♀️ሰላም ለዝክረ ስምክ፡- በዃለኛው ዘመን የዚህን ዓለም ረሃብና ጥም የሚያስረሳና ከወይን ዘለላ ይልቅ ለሚወደድ ስም አጠራርህ ሰላምታ ይገባል፡፡ ህጻን የሆነ የማርያም ልጅ ወዳጅ ጻድቁ አባቴ አቡነ ሀብተ ማርያም ሆይ በቦታው ታርፍለት ዘንድ ጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት አጥብቆ እንደ ለመነ እኔም አገልጋይ ከሀዘን ሁሉ ታድነኝና በቤቴም ታርፍ ዘንድ እለምነሃለሁ፡፡
🔔የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን ::
🙇♀️አምላከ አቡነ ሀብተማርያም ሆይ እኛን ሁላችንን ከተቃጣ መዓት ከታዘዘ መቅሰፍት ከድንገተኛ ሞት ሰውረን ለዘለዓለሙ አሜን::
🔔 #ታላቅ_የጉባኤ_ጥሪ
“ዝክረ ጻድቅ ለዓለም ይሄሉ፡፡”መዝ 111/112፡6
የተከበራችሁ የጻድቁ ወዳጆች እንኳን በጤንነት በሕይወት ጠብቆ ለአቡነ ሀብተ ማርያም ዓመታዊ በዓል አደረሰን:: የጻድቁ አባታችንን በረከት ለመካፈል በ ኅዳር 26 ቀን ለነፍሳችን ቀለብ የሚሆኑ መርሐግብሮች ስለተዘጋጁ በዕለቱ ተገኝተው ከበዓሉ ተካፋይ እንዲሆኑ ተጋብዘዎል::
😇የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን ::
“ዝክረ ጻድቅ ለዓለም ይሄሉ፡፡”መዝ 111/112፡6
የተከበራችሁ የጻድቁ ወዳጆች እንኳን በጤንነት በሕይወት ጠብቆ ለአቡነ ሀብተ ማርያም ዓመታዊ በዓል አደረሰን:: የጻድቁ አባታችንን በረከት ለመካፈል በ ኅዳር 26 ቀን ለነፍሳችን ቀለብ የሚሆኑ መርሐግብሮች ስለተዘጋጁ በዕለቱ ተገኝተው ከበዓሉ ተካፋይ እንዲሆኑ ተጋብዘዎል::
😇የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን ::
December 4, 2020
ጻድቁ አቡነ ሀብተ ማርያም pinned a photo
#አቡነ_ሀብተ_ማርያም_ጻድቅ ኅዳር ፳፮
✞ “ዝክረ ጻድቅ ለዓለም ይሄሉ፡፡” (“የጸድቅ መታሰቢያ ለዘላለም ይኖራል፡፡” መዝ 111/112፡6)
✞ እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም የዕረፍት መታሰቢያ በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደረሳችሁ አሜን፡፡
=>እኒህ ጻድቅ የሃገራችን ኮከበ ገዳም ናቸው:: "ጽድቅና ትሩፋት እንደ ሃብተ ማርያም" እንዲሉ አበው:: ባሕር ከሆነ ጣዕመ ሕይወታቸው ጥቂቱን ለበረከት እንካፈል::
+ጻድቁ መካነ ሙላዳቸው ሽዋ (የራውዕይ) ውስጥ ሲሆን አባታቸው ፍሬ ቡሩክ: እናታቸው ደግሞ ቅድስት ዮስቴና ትባላለች:: በተለይ ቅድስት ዮስቴና እጅግ ደመ ግቡ: ምጽዋትን ወዳጅ: ቡርክት ሴት ነበረች:: እንዲያውም ከጻድቁ መወለድ በፊት መንና ጭው ካለ በርሃ ገብታ ነበር::
+ግን የበቃ ግኁስ አግኝቷት "ከማሕጸንሽ ደግ የሥላሴ ባርያ አለና ተመለሽ" ብሏት እንደ ገና ተመልሳለች:: ጻድቁን ወልዳ አሳድጋም እንደ ገና መንና በተጋድሎ ኑራ 7 አክሊላትን ተቀብላ ዐርፋለች::
+ወደ ጻድቁ ዜና ሕይወት ስንመለስ አቡነ ሃብተ ማርያም ገና ሕጻን እያሉ ከእናታቸው ጋር ቆመው ሲያስቀድሱ "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" ሲባል ይሰማሉ:: ይሕችን ጸሎት በሕጻን አንደበታቸው ይዘው ሌሊት ሌሊት እየተነሱ "ማረን እባክህን?" እያሉ ይሰግዱ ነበር::
+የ5 ዓመት ሕጻን እንዲህ ሲያደርግ ማየቱ በእውነት ይደንቃል:: ትንሽ ከፍ ብለው በእረኝነት ሳሉም ፍጹም ተሐራሚና ጸዋሚ ነበሩ:: ጸጋው ስለ በዛላቸውም ልጅ ሆነው ብዙ ተአምራትን ሰርተዋል:: የፈጣሪውን ስም ያቃለውን አንድ እረኛም በዓየር ላይ ሰቅለው አውለውታል::
+ከዚያ ግን ለአካለ መጠን ሲደርሱ ወደ ት/ቤት ገብተው: መጻሕፍትንም አጥንተው መንነዋል:: በአባ መልከ ጼዴቅ እጅ ከመነኮሱ በሁዋላ የሠሩትን ትሩፋትና የነበራቸውን ተጋድሎ ግን የኔ ብጤ ደካማ ሰው ሊዘረዝረው አይችልም::
*ባሕር ውስጥ ሰጥመው 500 ጊዜ ይሰግዳሉ::
*በየቀኑ 4ቱን ወንጌልና 150 መዝሙረ ዳዊትን ይጸልያሉ:: (መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ታላቅ ጸሎት ነው)
*በ40 ቀናት: ቀጥሎም በ80 ቀን አንዴ ብቻ ይመገባሉ::
*ምግባቸው ደግሞ ሣርና ቅጠል ብቻ ነው::
*በየዕለቱ ያለ ማስታጐል ማዕጠንት ያሳርጋሉ:: (ካህን ናቸውና)
*ዘወትር በንጽሕና ቅዱስ ሥጋውን ይበላሉ: ክቡር ደሙን ይጠጣሉ::
*በፍጹም በልባቸው ውስጥ ቂምን: መከፋትን አላሳደሩም::
+በእነዚህና በሌሎች ትሩፋቶቻቸው ደስ የተሰኘ ጌታም ለጻድቁ የእሳትና የብርሃን ሠረገላን ሰጥቷቸው በዚያ እየበረሩ ኢየሩሳሌም ይሔዱ ነበር:: ከብዙ የተጋድሎ ዘመናት በሁዋላም የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ አዕላፍ መላእክትን አስከተትሎ መጥቶ አላቸው::
+"*ስለ እኔ ረሃብና ጥምን ስለ ታገስክ: *ስለ ምናኔሕ: *ስለ ተባረከ ምንኩስናህ: *ስለ ንጹሕ ድንግልናህ: *ቂምና በቀልን ስላለመያዝህ: *ስለ ንጹሕ ክህነትህና ማዕጠንትህ: *ቅዱስ ወንጌልን በፍቅር ስለ ማንበብህ 7 አክሊላትን እሰጥሃለሁ::"
+"በሰማይም ከመጥምቁ ዮሐንስ ጐን: 500 የእንቁ ምሰሶዎች ያሉበትን አዳራሽ ሰጥቼሃለሁ:: በስምህ የሚለምኑ: በቃል ኪዳንህ የሚማጸኑትንም ሁሉ እንድምርልህ 'አማንየ! በርእስየ!' ብዬሃለሁ" አላቸው::
+ቅዱሳን መላእክትም "ሃብተ ማርያም ወንድማችን" ሲሉ አቀፏቸው:: ጌታ ግን በዚያች ሰዓት አንድም ሦስትም ሆኖ ታያቸውና አቅፎ 3 ጊዜ ሳማቸው:: ከፍቅሩ ጽናትም የተነሳ ነፍሳቸው ከሥጋቸው ተለየች:: በዝማሬም ወሰዷት::
~
✞ ሰላም ለመቃብሪከ ከፀሎትና ከገል ብዛት የተነሳ እግሩ የተሰበረ የአባታችን የተክለ ሃይማኖት ገዳም በሆኑት ደብረ ሊባኖስ ውስጥ ለሆነች መቃብርህ ሰላምታ ይገባል:: ጻድቁ አባቴ ሃብተማርያም ሆይ
ሩጫቸውን የጨረሱ የኤልሳና የፊልጻስ ስማቸው በፈጣሪያቸው ዘንድ በአምደ ወርቅ እንደተጻፈ ያንተም ስም እንደእነሱ የተፃፈ ነው እነሆ እነሱ በምግባር በሃይማኖት የተስማሙ ናቸዉና::
✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞
✞ ወለወላዲቱ ድንግል ✞
✞ ወለመስቀሉ ክቡር አሜን ✞
✞ “ዝክረ ጻድቅ ለዓለም ይሄሉ፡፡” (“የጸድቅ መታሰቢያ ለዘላለም ይኖራል፡፡” መዝ 111/112፡6)
✞ እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም የዕረፍት መታሰቢያ በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደረሳችሁ አሜን፡፡
=>እኒህ ጻድቅ የሃገራችን ኮከበ ገዳም ናቸው:: "ጽድቅና ትሩፋት እንደ ሃብተ ማርያም" እንዲሉ አበው:: ባሕር ከሆነ ጣዕመ ሕይወታቸው ጥቂቱን ለበረከት እንካፈል::
+ጻድቁ መካነ ሙላዳቸው ሽዋ (የራውዕይ) ውስጥ ሲሆን አባታቸው ፍሬ ቡሩክ: እናታቸው ደግሞ ቅድስት ዮስቴና ትባላለች:: በተለይ ቅድስት ዮስቴና እጅግ ደመ ግቡ: ምጽዋትን ወዳጅ: ቡርክት ሴት ነበረች:: እንዲያውም ከጻድቁ መወለድ በፊት መንና ጭው ካለ በርሃ ገብታ ነበር::
+ግን የበቃ ግኁስ አግኝቷት "ከማሕጸንሽ ደግ የሥላሴ ባርያ አለና ተመለሽ" ብሏት እንደ ገና ተመልሳለች:: ጻድቁን ወልዳ አሳድጋም እንደ ገና መንና በተጋድሎ ኑራ 7 አክሊላትን ተቀብላ ዐርፋለች::
+ወደ ጻድቁ ዜና ሕይወት ስንመለስ አቡነ ሃብተ ማርያም ገና ሕጻን እያሉ ከእናታቸው ጋር ቆመው ሲያስቀድሱ "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" ሲባል ይሰማሉ:: ይሕችን ጸሎት በሕጻን አንደበታቸው ይዘው ሌሊት ሌሊት እየተነሱ "ማረን እባክህን?" እያሉ ይሰግዱ ነበር::
+የ5 ዓመት ሕጻን እንዲህ ሲያደርግ ማየቱ በእውነት ይደንቃል:: ትንሽ ከፍ ብለው በእረኝነት ሳሉም ፍጹም ተሐራሚና ጸዋሚ ነበሩ:: ጸጋው ስለ በዛላቸውም ልጅ ሆነው ብዙ ተአምራትን ሰርተዋል:: የፈጣሪውን ስም ያቃለውን አንድ እረኛም በዓየር ላይ ሰቅለው አውለውታል::
+ከዚያ ግን ለአካለ መጠን ሲደርሱ ወደ ት/ቤት ገብተው: መጻሕፍትንም አጥንተው መንነዋል:: በአባ መልከ ጼዴቅ እጅ ከመነኮሱ በሁዋላ የሠሩትን ትሩፋትና የነበራቸውን ተጋድሎ ግን የኔ ብጤ ደካማ ሰው ሊዘረዝረው አይችልም::
*ባሕር ውስጥ ሰጥመው 500 ጊዜ ይሰግዳሉ::
*በየቀኑ 4ቱን ወንጌልና 150 መዝሙረ ዳዊትን ይጸልያሉ:: (መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ታላቅ ጸሎት ነው)
*በ40 ቀናት: ቀጥሎም በ80 ቀን አንዴ ብቻ ይመገባሉ::
*ምግባቸው ደግሞ ሣርና ቅጠል ብቻ ነው::
*በየዕለቱ ያለ ማስታጐል ማዕጠንት ያሳርጋሉ:: (ካህን ናቸውና)
*ዘወትር በንጽሕና ቅዱስ ሥጋውን ይበላሉ: ክቡር ደሙን ይጠጣሉ::
*በፍጹም በልባቸው ውስጥ ቂምን: መከፋትን አላሳደሩም::
+በእነዚህና በሌሎች ትሩፋቶቻቸው ደስ የተሰኘ ጌታም ለጻድቁ የእሳትና የብርሃን ሠረገላን ሰጥቷቸው በዚያ እየበረሩ ኢየሩሳሌም ይሔዱ ነበር:: ከብዙ የተጋድሎ ዘመናት በሁዋላም የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ አዕላፍ መላእክትን አስከተትሎ መጥቶ አላቸው::
+"*ስለ እኔ ረሃብና ጥምን ስለ ታገስክ: *ስለ ምናኔሕ: *ስለ ተባረከ ምንኩስናህ: *ስለ ንጹሕ ድንግልናህ: *ቂምና በቀልን ስላለመያዝህ: *ስለ ንጹሕ ክህነትህና ማዕጠንትህ: *ቅዱስ ወንጌልን በፍቅር ስለ ማንበብህ 7 አክሊላትን እሰጥሃለሁ::"
+"በሰማይም ከመጥምቁ ዮሐንስ ጐን: 500 የእንቁ ምሰሶዎች ያሉበትን አዳራሽ ሰጥቼሃለሁ:: በስምህ የሚለምኑ: በቃል ኪዳንህ የሚማጸኑትንም ሁሉ እንድምርልህ 'አማንየ! በርእስየ!' ብዬሃለሁ" አላቸው::
+ቅዱሳን መላእክትም "ሃብተ ማርያም ወንድማችን" ሲሉ አቀፏቸው:: ጌታ ግን በዚያች ሰዓት አንድም ሦስትም ሆኖ ታያቸውና አቅፎ 3 ጊዜ ሳማቸው:: ከፍቅሩ ጽናትም የተነሳ ነፍሳቸው ከሥጋቸው ተለየች:: በዝማሬም ወሰዷት::
~
ሩጫቸውን የጨረሱ የኤልሳና የፊልጻስ ስማቸው በፈጣሪያቸው ዘንድ በአምደ ወርቅ እንደተጻፈ ያንተም ስም እንደእነሱ የተፃፈ ነው እነሆ እነሱ በምግባር በሃይማኖት የተስማሙ ናቸዉና::
✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞
✞ ወለወላዲቱ ድንግል ✞
✞ ወለመስቀሉ ክቡር አሜን ✞
December 6, 2020
ጻድቁ አቡነ ሀብተ ማርያም pinned «https://www.youtube.com/watch?v=pFJSyHOdu1s&feature=share»
🕊“በዚያን ጊዜ ጻድቃን በአባታቸው መንግሥት እንደ ፀሐይ ይበራሉ። የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ።”ማቴ13:43
✞ እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም
በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደረሳችሁ አሜን፡፡
♥️"የዕጣንህ ሽታ የሎሚ በረከት
ከጭንቅ አሻግሮኛል በቸገረኝ ሰዓት
ናፈቀኝ ገዳሙ የኪዳንህ ስፍራ
ሰንሰለቴ ወልቋል ስምህን ስጠራ"
✞ የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን ::
✞ ✞ አምላከ አቡነ ሀብተማርያም ሆይ እኛን ሁላችንን ከተቃጣ መዓት ከታዘዘ መቅሰፍት ከድንገተኛ ሞት ሰውረን ለዘለዓለሙ አሜን ✞ ✞
✞ እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም
በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደረሳችሁ አሜን፡፡
♥️"የዕጣንህ ሽታ የሎሚ በረከት
ከጭንቅ አሻግሮኛል በቸገረኝ ሰዓት
ናፈቀኝ ገዳሙ የኪዳንህ ስፍራ
ሰንሰለቴ ወልቋል ስምህን ስጠራ"
✞ የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን ::
✞ ✞ አምላከ አቡነ ሀብተማርያም ሆይ እኛን ሁላችንን ከተቃጣ መዓት ከታዘዘ መቅሰፍት ከድንገተኛ ሞት ሰውረን ለዘለዓለሙ አሜን ✞ ✞
January 4
🌹እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደረሳችሁ አሜን:፡
🌷ኦ ሚካኤል እግዚእየ ወፍቁርየ ኢትጸመመኒ ወኢትግድፈኒ ውስተጽምዕ ወይኩን ዘአልቦ ረዳኢ::ወሶቤሃ መጽኡ ኅቤሁ 7ቱ ሊቃነ መላእክት እንዘ ሚካኤል ቅድሜሆሙ የሐውር::..."ገድለ አቡነ ሀብተ ማርያም ዘይትነበብ በዕለተ ረቡዕ
🌼የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን ::
🌸ሰላም ለልብከ ለቃለ መጻህፍት ምዕራፍ ::ዘበውስቴታ ይትረከብ መራኁተ ጽድቅ ዘእደ ኬፋ::ሀብተ ማርያም መልአክ ዓቃቤ ትእዛዙ ለአልፋ ይሡቀኒ እምትንታኔ አልብየ ተስፋ::ጸውዖ ስምከ ዘአልቦ ዘለፋ::
🌺ጻዲቁ አቡነ ሀብተማርያም በፈሪሃ እግዚአብሔር በትምህርት አደገ፡፡ ከዕለታት በአንድ ቀን ካህናቱ በቤተክርስቲያን ምህላ ሲያደርሱ "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" እያሉ ሲፀልዩ ሰምቶ በልቡናው ይህች ፀሎት በጣም ጥሩና መልካም ፀሎት ናት አለ በዚህ ፀሎት ከዓለም አሳችነት ከገሃነም እሳት እንድንባት ዘንድ አውቃለሁ የንስሐ መንገድ ናት ብሎ ተናገረ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም በዚህች ፀሎት ተጠምዶ በጾምና በፀሎት በስደት የሚኖር ሆነ::
🌻ኦ አምላከ አቡነ ሀብተ ማርያም ዕቀቦ ወአድኅኖ ወባልሆ እመከራ ሥጋ ወነፍስ ወእምኩሉ ተቃራኒ ወእምኩልነ ክቡር ሀብተ ማርያም ለዓለም ዓለም አሜን ለይኩን ለይኩን::
🌷ኦ ሚካኤል እግዚእየ ወፍቁርየ ኢትጸመመኒ ወኢትግድፈኒ ውስተጽምዕ ወይኩን ዘአልቦ ረዳኢ::ወሶቤሃ መጽኡ ኅቤሁ 7ቱ ሊቃነ መላእክት እንዘ ሚካኤል ቅድሜሆሙ የሐውር::..."ገድለ አቡነ ሀብተ ማርያም ዘይትነበብ በዕለተ ረቡዕ
🌼የጻድቁ አባታችን የሀብተማርያም ልጆች ሆይ በማስተዋል እና በማገናዘብ በዓላቶቹን አክብሩ በጠዋት እና በማታም ያለመታከት ምስጋናን አቅርቡ የእግዚአብሔር ክብር ሁሌ በሱ ላይ ይገለጻል እና ቃል ኪዳኑም ለዘለዓለም ተስፍ ይሁነን ::
🌸ሰላም ለልብከ ለቃለ መጻህፍት ምዕራፍ ::ዘበውስቴታ ይትረከብ መራኁተ ጽድቅ ዘእደ ኬፋ::ሀብተ ማርያም መልአክ ዓቃቤ ትእዛዙ ለአልፋ ይሡቀኒ እምትንታኔ አልብየ ተስፋ::ጸውዖ ስምከ ዘአልቦ ዘለፋ::
🌺ጻዲቁ አቡነ ሀብተማርያም በፈሪሃ እግዚአብሔር በትምህርት አደገ፡፡ ከዕለታት በአንድ ቀን ካህናቱ በቤተክርስቲያን ምህላ ሲያደርሱ "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" እያሉ ሲፀልዩ ሰምቶ በልቡናው ይህች ፀሎት በጣም ጥሩና መልካም ፀሎት ናት አለ በዚህ ፀሎት ከዓለም አሳችነት ከገሃነም እሳት እንድንባት ዘንድ አውቃለሁ የንስሐ መንገድ ናት ብሎ ተናገረ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም በዚህች ፀሎት ተጠምዶ በጾምና በፀሎት በስደት የሚኖር ሆነ::
🌻ኦ አምላከ አቡነ ሀብተ ማርያም ዕቀቦ ወአድኅኖ ወባልሆ እመከራ ሥጋ ወነፍስ ወእምኩሉ ተቃራኒ ወእምኩልነ ክቡር ሀብተ ማርያም ለዓለም ዓለም አሜን ለይኩን ለይኩን::
February 3
🕊እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደረሳችሁ አሜን:፡
https://www.youtube.com/watch?v=_5APlmAq2MY&feature=share
https://www.youtube.com/watch?v=_5APlmAq2MY&feature=share
YouTube
መልክአ አቡነ ሃብተ ማርያም ለመማሪያ ይሆን ዘንድ የተዘጋጀ በሊቀ ካህናት ነቅዓ ጥበብ የማነ ብርሃን
March 5
🤍 ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በግርማ መንግስቱ ሲመጣ "ቅዱሳን በዓለም ላይ እንደሚፈርዱ አታውቁምን?" 1ቆሮ6:2
††እንኳን ለዓብይ ጾም እኩሌታ እንዲሁም ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደሰችሁ†
🤍"ሰላም ለከናፍሪከ ማዕፆ ትእግስት ዘሤማ ሀብተ ማርያም ሚናስ ሱታፌ መላእክት ዘራማ: ዓማዴ ሰማይ ክርስቶስ አመ ይመጽእ በግርማ:: ነፍሰ ዚአየ በትንባሌከ አስተሳልማ:: እስመ ሰሉሥ ቅድሜሁ ለፌማ::"
“❤️ፍቅር ያገብረኒ ነጊረ ዜናሆሙ ለቅዱሳን❤️” አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
🕊በአለም የተበተኑ በጏች የተባሉ ልጆችህ የሚጠበቅበት የእምነት ዘንግን ለጨበጠ መሐል እጅህ ሰላምታ ይገባል::ጻድቁ አባቴ ሀብተማርያም ሆይ የዚች አለም ጸጥታዋና ሰላሟ አንተ ነህ እኮ እኔን ለመውደቅ የተፍገመገምኩትን እንደብረት ዘንግ የሆነ ጸሎትህ ከወደቅኩበት መሬት ያንሳኝ ይደግፈኝ ሁለተኛም የጏሰቆለች ነፍሴን ቃልኪዳንህ አይለያት::(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)
🤲ኦ አምላከ አቡነ ሀብተ ማርያም ዕቀቦ ወአድኅኖ ወባልሆ እመከራ ሥጋ ወነፍስ ወእምኩሉ ተቃራኒ ወእምኩልነ ክቡር ሀብተ ማርያም ለዓለም ዓለም አሜን ለይኩን ለይኩን::
መልክአ አቡነ ሀብተማርያም በዜማ 👉https://www.youtube.com/watch?v=_5APlmAq2MY&feature=share
††እንኳን ለዓብይ ጾም እኩሌታ እንዲሁም ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደሰችሁ†
🤍"ሰላም ለከናፍሪከ ማዕፆ ትእግስት ዘሤማ ሀብተ ማርያም ሚናስ ሱታፌ መላእክት ዘራማ: ዓማዴ ሰማይ ክርስቶስ አመ ይመጽእ በግርማ:: ነፍሰ ዚአየ በትንባሌከ አስተሳልማ:: እስመ ሰሉሥ ቅድሜሁ ለፌማ::"
“❤️ፍቅር ያገብረኒ ነጊረ ዜናሆሙ ለቅዱሳን❤️” አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
🕊በአለም የተበተኑ በጏች የተባሉ ልጆችህ የሚጠበቅበት የእምነት ዘንግን ለጨበጠ መሐል እጅህ ሰላምታ ይገባል::ጻድቁ አባቴ ሀብተማርያም ሆይ የዚች አለም ጸጥታዋና ሰላሟ አንተ ነህ እኮ እኔን ለመውደቅ የተፍገመገምኩትን እንደብረት ዘንግ የሆነ ጸሎትህ ከወደቅኩበት መሬት ያንሳኝ ይደግፈኝ ሁለተኛም የጏሰቆለች ነፍሴን ቃልኪዳንህ አይለያት::(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)
🤲ኦ አምላከ አቡነ ሀብተ ማርያም ዕቀቦ ወአድኅኖ ወባልሆ እመከራ ሥጋ ወነፍስ ወእምኩሉ ተቃራኒ ወእምኩልነ ክቡር ሀብተ ማርያም ለዓለም ዓለም አሜን ለይኩን ለይኩን::
መልክአ አቡነ ሀብተማርያም በዜማ 👉https://www.youtube.com/watch?v=_5APlmAq2MY&feature=share
YouTube
መልክአ አቡነ ሃብተ ማርያም ለመማሪያ ይሆን ዘንድ የተዘጋጀ በሊቀ ካህናት ነቅዓ ጥበብ የማነ ብርሃን

No comments:
Post a Comment